እርጥብ ማህፀኗ ~ ሚሊዮኖች ያፈራ ።
ተረግማ እንደው እንጃ ~ ወይ አንሷት ምርቃት
ይኸው ስንት ዘመን ~ መከራ ‘ሚንጣት
፧
አለች አንዲት እናት
፧
ወልዳ የመከነች
ከብዳ የቀለለች
አምና የናቀች
ኖሯት የደኸየች
፧
]አንዲት እናት አለች
፧
ለምለም አፈሯ ላይ ~ ቂም እየተዘራ
ልጆቿ እያጭዱ ~ የበቀል አዝመራ
ለፍቅር ተኮንና ~ ጥላቻን ‘ምትሰፍር
የተፈረደባት ~ ደም ገብራ እንድትኖር
፧
አለች አንዲ አንዲት
፧
ጠግባ የተራበች
ሰብታ የሞገገች
ሰፍታ የጠበበች
፧
አንዲት እናት አለች
፧
ቀዳሚ ታሪኳ ~ በክፋት ደብዝዞ
የንፉቅቅ የምትሄድ ~ በኋልዮሽ ጉዞ
የስልጣኔ አልፋ ~ በኩር እንዳልነበረች
ችሮትን ጠባቂ ~ ቀላዋጭ የሆነች
፧
አንዲት እናት አለች
፧
ነቅታ ያንቀላፋች
ቀንታ የጎበጠች
ከብራ የወደቀች
ፈክታ የጠቆረች
፧
አንዲት እናት አለች
፧
ዘ-ል-ዝ-ለ-ው………..
በ
ል
ተ
ው
…………………………
በልተው ሊጨርሷት ~ አንድ ሃሙስ የቀራት
፧
አለች ምስኪን እናት
፧
ፍቅርን ተጠምታ ~ ፍቅርን ተርባ
ሳቋን ተቀምታ ~ ሃዘን ተከናንባ
ጉልበቷን ታቅፋ ~ ደም የምታነባ
፧
ከአምናው ፣ አቻምናው ~ ዘንድሮ ብሶባት
ስቃይ የምታምጥ ~ ፈውስ የቸገራት
፧
አለች አንዲት እናት!!
==============
አሁንስ እኔ ‘ንጃ
እንጃ ፈርቻለሁ
እንጃ ሰግቻለሁ ~ በርትቷል ስቃይዋ
ደመና ውጦታል ~ ዙፋነ ሰማይዋ ።
፣
አሁንስ እኔ ‘ንጃ
እንጃ ሰግቻለሁ
፣
የቀስተደመና ~ አምሳል ምልክቷ
የሷነት መለያ ~ ግምጃ መቀነቷ
ላልቶ አይቻለሁ !!
፧
አሁንስ እኔ ‘ንጃ
እንጃ ፈርቻለሁ !!
፣
እንጃ ሰግቻለሁ ~ ለዝች “መካን” እናት
ኪዳንዋን አስቦ ~ ፈጣሪ ካልረዳት
በዛሬ ስቃይዋ
ፈራሁ ለነገዋ
ዋ!!!
የእፉኝቶች እናት!... (አስሜክስ)
Filed in: Amharic