>

ኦሮማራ “መርህ አልባ ጉድኝት” (ስዩም ተሾመ)

አንድ ጥያቄ አለኝ ጓዶች፤ “መርህ -አልባ-ጉድኝት” ምን ማለት ነው? ይህ “መርህ አልባ ጉድኝት” ተፈጠረ የተባለው በአህአዴግ አባል ድርጅቶች ከፍተኛ አመራሮች መካከል ነው። ድርጅቶቹ ኦህዴድና ብአዴን እንደሆኑ መገመት ቀላል ነው። “ጉድኝት” የሚለው ቃል ደግሞ “ጓድ፥ ጓደኛ፥ ጓደኝነት፥ ባልንጀራ፣ ግንኙነት፥ መቀራረብ፥ አብሮነት፥ አንድነት፥…” እንደማለት ነው። ስለዚህ “መርህ አልባ ጉድኝት” የተባለው ከቅርብ ግዜ ወዲህ እየታየ ያለው የኦሮማራ የትብብርና አንድነት ነው። መልካም፣…በሁለቱ ክልል አመራሮች፣ ሕዝቦችና ምሁራን መካከል ያለው “ጉድኝት” “መርህ አልባ” ያለው የፖለቲካ ቡድን የሚመራበት ትክክለኛው መርህ ምንድነው? በእርግጥ “ጉድኝት/ጓደኝነት/ግንኙነት” መህር-አልባ ከሆነ “መለየት/መለያየት/#አፓርታይድ” – “Separation/Separateness/#Apartheid” ትክክለኛው መርህ ይሆናል። እኛስ ምን አልን ታዲያ? ህወሓት/ኢህአዴግ “የኦሮሞና አማራ ሕዝቦችን በመለያየት ላይ የተመሰረተ የአፓርታይድ ስርዓት ነው” የምንለው እኮ ለዚህ ነው። አሁንም በድጋሜ የምንለው ነገር የኦሮማራ ጥምረት መሰረታዊ ዓላማ #የህወሓትን_የበላይነት ማስወገድ ነው። በሁለት ሕዝቦች ትብብርና ጉድኝት አይኑ የሚቀላ የፖለቲካ ቡድን ህወሓትና ህወሓት ብቻ ነው።

Filed in: Amharic