>
5:14 pm - Monday April 30, 6649

ከጠቅላይ ምኒስትሩ እንቶ ፈንቶ ተረቶች ጀርባ ያሉ መልእክቶች...!!! የመጨረሻ ክፍል (መር እድ እስጢፋኖስ)

ከጠቅላይ ምኒስትሩ እንቶ ፈንቶ ተረቶች ጀርባ ያሉ መልእክቶች…!!! የመጨረሻ ክፍል
መር እድ እስጢፋኖስ

ኢትዮጵያ ሀገራችን ወጣት መርዎች የተፈራቀባት ሀገር ነች፤
ለምሳሌ:-
     # መንግስቱ ሀይለማርያም ስልጣን ስይዙ እድሜያቸው 37 ነበረ።
#   መለስ ዜናዊ ስልጣን ሲይዝ 30 አመታቸው ነበረ።
#  ሀይለማርያም ደሳለኝ ስልጣን ሲይዙ 53 አመታቸው ነበረ።
#  አብይ አህመድ ስልጣን ስይዙ 42 አመታቸው ነው።

ሁሉም የየራሳቸው ድክመት እና ጥንካሬ ይኖራቸዋል። ወደዛ አንገባም ተራ ሰዋዊ ባህሪን አንስተን ግን ጥቂት እንላለን።አሁን በስልጣን ላይ ስላሉት  አብቹ  ያለፈው ሳምንት የጀመርነውን የሚይሣዩትን ያልተገባ መሪን የማይመጥን ባህሪ/ childish mailiting act/ ማየት እንቀጥላለን።
ሁሉም መሪዎቻቻን በባህሪ አንድ የሚያደርጋቸው ነገር አለ። ስለራሳቸው ጥሩም ይሁን መጥፎ ስራቸው ብዙም እንዲወራ አይፈልጉም ።
በተለይም በግል ስለሰሩት  ስለጥሩ ስራቸው እንዲወራ አይፈልጉም በሆነ አስገዳጅ ሁኔታ ከተወራ የቡድን ስራ ….የጋራ ስራ ተደርጎ እንዲታይ ያደርጋሉ እንጂ የራሳቸው የማድረግ ዝንባሌ አይታይባቸውም.. .. . ይሄም ኢትዮጵያዊ ጨዋነት የሚባል ስነምግባርን ያሳያል።
እንግዲህ ስልጣን ላይ ሲወጡ በእድሜ በጣም ትንሹ መለስ ዜናዊ ናቸው።መለስ ዜናዊ በግሌ ከማይቀበሏቸው ስዎች ውስጥ ብሆንም በአነገገር ሲመጣ አክባሪያቸው ነኝ። በአስተሳሰብ ሲመጣ ዘመን የተሻገሩ ሆነው አገኝቸዋለሁ (ከነክፋታቸው)።
እንደ መለስ ዜናዊ አይነት ሰውን የለመደች ሀገር (በአነጋገር ነው አሁንም) እንደ ጠ/ሚ አብይ አህመድ አይነት የህፃን ባህሪ የሚታይበት መሪ ላይ መውደቅ መገመት  ማመንም ይከብዳል።
ጠ/ሚ አብይ አህመድ
ስለራሳቸው አውርተው አይጠግቡም። አንድ መድረክም ይሁን እስካሁን ባገኙት በመቶዎች መድረክ ስለራሳቸው የማያወሩበት አጋጣሚ የለም።አስቂኝ  የሚያደርገው ታዲያ ስለራሳቸው የሚያወሩር ነገሮች የሚያስከብራቸው ወይም የሚያስደንቃቸው ወይም ለሌላ ወጣት አርአያ የሚደርጋቸው ሳይሆን ራሳቸውን መቀለጃ እያደረጋቸው ይገኛል እንጠቅሳለን…
እርቲ ቡርቲ  ወሪያቸው ማየት እንቀጥል።
ስለልጅነታቸው ማውራት ለምን ይወዳሉ?
የሳቸው የልጅነት አስተዳደግ መቼም እንደ ሮቦት ነው። ሱቅ ስላክ የቆመውን መኪንና “ቩቭ” አድርጌ አስነሳንና የተላኩትን ገዝቼ እመለሳለሁ አሉ ።ልጅ እያሉ መኪና እንደከብት በሚትራመስባት በሻሻ  ከተማ ነበረች።በበሻሻ  ከተማ ደግም “ህፃናቶች ይንዱ አትከልክሏቸው በሚባልባት”የትራፊክ ህግ ነበረ አሉ በበሻሻ ከተማ …አርቲ ቡርቲ( መልክቱ ምንድነው በልጅነቴ ጀምሮ ልዩ ነኝ ነው)
በልጅነቴ ድሪም አረግ ነበር እናቴ በሰባት አመቴ ሰባተኛው ንጉስ ትሆናለህ  ብላኝ ስለነበር ይኸው ጠ/ሚ ሆንኩኝ።
አንድ ወቅት ቴክ(ተክኖሎጂ) አዘጋጅ የሆው ጋዜጠኛ ሰለምን ጠ/፡ሚ ጠየቀ።”የቴክኖሎጂን ትራንስፎርሚአሽን እንዴት ያዩታል”በኢትዮጵያ
መልስ ስጡ ነብዩ አብይ….ለምሳሌ እኔ ቤተመንግስቱን ስረከብ የጠቅላይ ሚንስትሩ ቢሮ ሽንትቤት አልነበረውም…….አሁን  ሽንት ቤት አለው።ባአለም ላይ የሚወዳደር ቢሮ አለን።ሌላ እንቶ ፈንቶ
መለመን መክሊቴ ነው ለምሳሌ ወደግልፍ አገሮች ሄጄ ገንዘብ ጠየኳቸው በቃ ወዲያው  ሰጡኝ።አብይ ምን ሰጥተው ? ……አይታወቅም። ስጦታ ነው የሚሉት ። ይሄ አሁን ወንጀል ነው።ኮራብትድ ሊደረጉ ይችላሉ።
በፈረንሳይ ህግ ሎክሶሎግጂ ይባላል።አንድ መሪ በምንም አይነት የገንዘብ ስጦታ መቀበል የለበትም ።የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኒኮላስ ሳርኮዚ ከሊቢያው ፕሬዝዳንት ሙአመር ጋዳፊ የገንዘብ ስጦታ በመቀበላቸው 3 አመት ተፈርዶባቸዋል ለንድ አመት ዘብጥያ ወርደዋል። ፥በአሜሪካ ኢሞልመንት የሚባል ህግ አለው።ቢያደርጉት እንኳ ወደ መንግስት ግምጃቤ ነው መግባት ያለበት።
በቻይና  የአፍሪካ መሪዎች ፎረም ተገኝተን ሳለን  ስለህዝብ ብዛት ከጣልያኑን መሪ  አወራንና 5 ሚልዬን ሰጠኝ..።አሉ አብይ አንድ ወቅት ይህ ንግግራቸው ሊበላችው አንደሚመጣ አያቀውም ማለት ይከብዳል።ነገር ግን ንጉስ ነኝ ማን ይከሰኛል ከሚል ህዝቡን ከመናቅ የሚመነጭ ነው። በቃ…. ፥የጉራ….ሌላ እንቶፈንቶ
በኢጋድ ስብሰባ ላይ….ሱዳን ሂጄ ኤርፖርት ስደርስ ዘነብ…. ኬንያ ሄጄ እንደዚሁ ዘነበ…ይኼው ዛሬም እዚህ ጅቡቲም ዘነበ….።ሌላ ሺሪ ሚሪ….እንዲህ እያልን ከዘለቅን ቀኑም አይበቃንም።
የጠቅላያችን እንዲህ እራስን የማሞካሽት እራስን ሱፐር ማን አርጎ ለማስየት የሚሄዱበት ርቀት ያተረፈላቸው ነገር  ትዝብትን፥ንቀትን እና መሳለቂያነተን ነው…… ወደ ፅሁፋችን መርነሻ ነጥብ እንነሳ ከነዚህ ንግግሮች ጅርባ የተፈለጉ መልእክቶች ምንድናቸው ነው…….?….? ከሾርት ሜሞርያችን ትንሽ እንወስዳለን።
ሁለት ምክንያቶ እናስቀድም…  የመጀመሪያው በራስ መተማመን ስለሌላቸው ነው።insecurity ስለሚሰማቸው ስለራሳቸው እያወሩ ለሌሎች መንገድ መስጠት አለባቸው(ያው እንደመደመር መንገድ ) መፍጠር።
ሁሉተኛው ደግሞ በራስ ፍቅር የተውሰዱ ስለሆነ  ያሉት ሙገሳዎች እና ማሞካሽቶች በቂ ሆኖ አያገኙትም።በምድር ላይ ያሉ ቃልቶች እንኳ እስኪያልቁ አድናቆት ቢፈስላቸው አይበቃቸውም።
በሳይንሱ ደግሞ ናርሲዝም የሚባል በሽታ ያሰቃያቸዋል (narcissistic ,narcissism )ተፈጥሮ።
ይህ አይነተ ባህሪያቸው ዋናው ምንጩ ሀይማኖታቸው ነው።ሀይማኖታቸው ለራሳቸሁ የከፍታ ቦታ ስጡ ይላል።”ለራሳቸሁን” አስቀድሙ የሚል አስተምህሮ እንዳለው በግልፅ ማስርዳት ይቻላል።
“የራሳችሁን በበጎ ምኞት” የራሳችሁ ምንነት አግዝፉ ይህን ስልጣን ሰጥቷችኋል በማለት ያስተምራሉ ።በመሆ ኑም ጠ/ሚ አብይ የዚህ መሰል ሰበካ ሰለባ መሆአቸው ማስርጃ ማቅረብ ይቻላል።
ሌላው ጠቅላያችን ከመቶ አመት በኋላ የናዝሬቱ “እየሱስ ክርስቶስ  በአለም ዙሪያ ለ 2 ሺ ዘመን ሲንከርተት ኖሮ  በመጨረሻ አራት ኩሎ ቤተ መንግስት ገባ እና አረፈ ብለው ያምናሉ”
ይህ በፖለቲካ ሂደት የመጣ ለውጥ ሳይሆን በተአምር የመጣ ነው ተብሎ እንዲታመን ከመፈለግ ይነሳል። ጠቅላያችን፦
ህፃንነቱ ጀምሮ በጣም የላቀ አስረሳሰብ የነበራቸው ጓደኞቹ አስተረማሪዎች ነበሩ ተንጠራቶ ያቅፋቸው ነበር ..የአራተ ኛ ክፍል እያሉ የ3ኛ ክፍል ፈተና ያርሙ ነበረ smart ከመሆናቸው የተነሳ..እና አሁን ዶክተር መሆኔን አትጠራጠሩ
ልመና ይሳካልኛል ከፈጣሪ የተቀባሁ በመሆኔ…..ባይ ናቸው ።እነዚህ ነገሮች በአብዛኛው ከሚያራምዱበት ሀይማኖትን እንደ ፖለቲካ ጎዳና ስለያዙት ነው።  ከሚታየው ይልቅ የማይታየውን ማመን ይመርጣሉ።..ከሚዳሰሰው ይልቅ የማይዳስሰውን የመቀበል ባህሪአቸው አድርገዋል።
ራሳቸውን ከመለኮት ጋር የሚያይዙበት ምክንያት ደግሞ አንድም ሀማኖተኛ ህዝብ ስለሆነ ከእግዚያቤር የተቀባነው የሚለውን “አየር ንብረት” ለመፍጠር በመፈለግ ነው።ይህም ለብዙ ነገር ሽፋን ይሰጣል።ሙስኛ ሆኖ ሳለ ዘመናዊ እምነት ተከታይ ነው አይሰርቅም የሚል መንፈስ ለመፍጠር የታለመ ነው።ለምሳሌ በአሁኑ ሰአት በአለም ባንክ አካውንታቸው እየተፈተሽ ያሉ ሁለት መሪዎች የቀድሞ የአንጎላ ፕሬዝዳንት ዶኦሴ ኤድዋርዶ ዶሳ ንቶስ እና  ጠ/ሚ አብይ አህመድ ናቸው።
አብዛኛው  በስልጣላይ የሚገኘ ኦሮሙማዎች የዘመናዊው እምነት ተከታይ  ናቸው።ኢሀዲግ በዘር ስትዘርፍ የነበረችበትን ስልት በአብይ  የመደመር ፍልስፍና “ሀይማኖትን ” ጨምረውበት እንድ ቁጥር ሊቦች ሆነው ሲያበቁ በክርስቶስ ስም ሽፋን ፍለጋ ወጥተዋል።  በተለይ ዘመናዊ ሀይማኖት  የሚሉት ሲሰርቅም ጥቅስ አላቸው.”በዝብዝ ብሎኛል ይላሉ”
ናሆም ም፥2ቁ9 (Nahum)
9፤” መዝገብዋ መጨረሻ የለውምና፥ የከበረውም የዕቃዋ ሁሉ ብዛት አይቈጠርምና ብሩን በዝብዙ፥ ወርቁንም በዝብዙ።” የሚለውን ጥቅስ ይጠቀማሉ።ኢስላማዊ ጀሀዲስቶችም ይህንን ነው የሚሉት”የክርስቲያንን ገንዘብ መዝረፍ ወይም መስረቅ የኛ ሀቅ ነው የሚሉት” የዛሬዎቹ መሪዎቻችን በጥቅ የታጠቁ ናችው።90 ፕርስንት አሁን ያሉ ባለሳልጣናት ፕሮቴስታንቶ ናቸው።አስገዳዮቸም ገዳዮቹም  ፕሮቴስታንቶች ናቸው።ጥቅስ ይዘዋል…….ለሁሉም ጥቅስ አላቸው።
ሲዋሹም ጥቅስ አላቸው”አብረሀምም ዋሽቷል”ይላሉ። ሲያሚነዝሩም ጥቅስ አላቸው።
በጥቅሉ እነዚህ.ዘመናዊ ሀይማኖቶች…”አለም በፅሀይ ዙሪያ ትሽከረከራለች።” “እግዚይስብሄር ደግሞ በነሱ ዙሪያ የሚሽከረከር ነው የሚመስላቸው” ሀይማኖቱ በራሱ ስብከቱ ….የለኝም አትበል ባይኖርህ እንኳ….አልችልም አትበል ባትችልም እንኳ ….የሚል አስትምሮት አላቸው።
በመሆኑም ጠቅላያችን በዚህ ቅዥት ውስጥ እየዋኙ እሳቸውና ተስፋቸው…..እንደሰማይና ምድር ተራርቋል። እሳቸውና የሚናገሩት  ቤት አልመታ ብሏል።
ከኔነት ድርና ማግ የተሰሩት ጠቅላያችን በስራ ከሚሳምኑን ይልቅ በመልኮት የተሰጡን መሪይችን አድርገን እንድናስብ መፈለጋቸው ዘመንን ወደዛሬ 70 አመት ወደኋላ ወስደውን በአባባ ጃንሆይ ዱካ ማለፍ የሚፈልጉ ሰው መስለው መታየት ብርቱ ጥረት ያደርጋሉ።
እግዲህ ጀማይካ ሄደው ራስ ተፈሪያን መፍጠር ባይችሉም ማዳጋስካር ሄደው ንጉስ አብቹ ነኝ ዘብሄረ ኦሮሙማ ቢሉ ለታሪክ ሽሚያው ለፍክክር መጥቀሙ አይቀርም።
ታሪክን መስራት እየቻሉ መንጠቅ ላይ ትኩረት አድርገው ያለመታከት እየሰሩ ነው።አብይ አህመድ ራሳቸውን ለማግነን የማይፈነቅሉት ድንጋይ የማይቧጥጡት ሰማይ የለም አሁንለታ እንኳ ” የእምዪ ምንይልክን ፎቶ አንስተው የራሳቸውን ፎቶ አሰቅለው ሲያበቃ የበሻሻ አድዋ ድል በአል” ከፊት አውራሪ ሽመልስ አብዲሳ እና ከቀኝ አዝማች ታዬ ደንዳአ ጋር በመስቀል አደባባይ ከቄሮ እና ከገዳ ጋር አክበረዋል።አገርን ያስገረመ ነበር ድርጊቱ። ….. እኛስ ግፋ ቢል እብደታቸው እንድስይባባስ እንፅልያለን በጣም ከበዛብን ንቀን እንተዋላን(ስለምንፈራ.)
ይሄ ክፉ አመላቸው ግን በቤት አልጋ ላይ እዳወድቅ ውጭ አደባብይም ሆነና…….ጎሮቢቶቻቸን ምሳደብ ጀመሩ እስኪ ጎሮቤት አገሮች በስድብ ካጠቃቀሱላቸው አንዳንዶቹን እንጠቅሳለን
* የኬንያውፕሬዝዳንት  ኦሁሩ ኬንያታ፦ ስቱፒድ ኪድቅ(stupid kid)ብሏቸዋል
* የሱማሌ ላንድ ፕሪዝዳንት ሙሴ ባሂ “ሙአረስ” ብለዋቸዋል
* የሱዳኑ ላእላይ ም/ቢት ጠባቂ (አብይ ፈረስና ጋሻ ከትግራይ ጦርነት አራት ቀን በፊት የሽለሟቸው) ጀነራል ቡርሀን።ውሽታም እብድ ።ሆስፒታል ይግባ ብለዋል።
* የኤርትራው መሪ ወዳጃቸው ኢሳያስ አፈውርቂ” ችኩል እና ስሜታዊ ብለዋቸዋል።መሪዎች  በአደባባይ በግልፅ የተሰደቡ መሪ ቢኖሩ ምንአልባት ጠ/ሚንስትር አብይ አህመድ አሊ የመጀሪያው ሳይሆኑ አይቀሩም።
የመሪ ባህሪ ያለመኖር፥ከእግር በላይ ጫማ ማድረግ፥በራስ ስሜትመነዳት የስከተለባቸው የዲፕሎማሲ ድምር ውጤት ይህን ይመስላል። አ ብ ቹ…..ነጋ ነጋ…. አብቹ ነጋ ነጋ…..ጀዲጋ!

Filed in: Amharic