አርአያ ተስፋማርያም
..በቤተመንግስት የእራት ግብዣ አቶ ታምራት ከተጠቀመጡበት ተነስተው መለስን በግል ለማናገር ተለዩና “መለስ ቂም የለኝም! ከአገር እሄዳለሁ። ስለፓርቲው ምንም አልልም። በማንኛውም ፓለቲካ ውስጥ አልገባም። አንድ ነገር ብቻ እለምንሃለሁ..አልሙዲ ቂመኛ ነው። ተከታትሎ እንዳይበቀለኝ ብቻ አድርግልኝ” ሲሉ ተማፀኑ። መለስ በታምራት ሀሳብ ተስማምተው የሼኹን ጉዳይ “በእኔ ተወው” አሉ። መለስ ጫማቸው ስር ተቀናቃኝ ያሉትን “ማስተኛት” ደስታ ይሰጣቸዋል። ..ታምራት ለሌሎቹም በፀሎት እንደሚያስቧቸው፣ የኢየሱስ አገልጋይ እንዲሆኑ ..ቡራኬ አሰምተው ግብዣው አለቀ። ..በዛ ሰሞን በግል ጋዜጦች የተጠየቁት ታምራት ፓለቲካ እርም ማለታቸውን፣ ከዚህ ይልቅ ስለኢየሱስና እርቅ እንደሚሰብኩ ተናገሩ። እርግጥ ነው በጣት ከሚቆጠሩት በቀር አብዛኞቹ የኢህአዴግ ባለስልጣናት “እግዚአብሔር የለም” ብለው ያምናሉ።..ታምራት ትንሽ ቆይተው አሜሪካ ዴንቨር መጡ። “ሼኹ እንዳይበቀለኝ” ያሉት 16 ሚሊዮን ዶላር በመንግስት ስም ተበድረው፣ በልጃቸው ስም ስዊዝ ባንክ በማስገባታቸው ነበር። አንድ ከፍተኛ የአቃቤ ህግ ሃላፊ በመንግስት ተወክለው ገንዘቡን ለማስመለስ ሄደው ነበር። ግን አልተሳካም። (ሃላፊው እዚህ ፌስቡክ አሉ..ዝርዝር መረጃ ማወቅ ከፈለጋችሁ በቅርብ ልመለስበት እችላለሁ.) አቶ ታምራት ያሳዘኑት ህዝብ ቢኖርም ይቅርታ ሳይጠይቁ እስካሁን አሉ። “እርቅና ስለኢየሱስ ብቻ እሰብካለሁ” ያሉት ታምራት ከዚህ ይልቅ በተቃራኒው መንገድ መታየታቸው ብዙዎችን አስገርሟል!..የመሰላቸውን ሀሳብ የመግለጽ መብት አላቸው! ቢሆንም ዘርና ጎጥ እየሳቡ “እከተለዋለሁ” ከሚሉት እምነት ጋር የሚጋጭና በተለይ የአምላክ ህግጋትን የሚጋፋ መርዝ መርጨት አስነዋሪ ነው ይላሉ ታዛቢዋች። በምስራቅ ኢትዮጵያ በእሳቸው ንግግር የተፈፀመውን ዘርና ብሄር የለየ ጥፋት ፍ/ቤት አልቀስው የተናገሩትን ..ዛሬ እረስተው ዳግም የጥፋት መርዘኛ ቃል መርጨት እጅግ አሳዛኝ ነው!