>
5:13 pm - Monday April 18, 2918

ወያኔ ፋሽስታዊ ጦር በሞያሌ ጭፍጨፋ ፈጸመ (እስራኤል ሰቦቃ)

ጨካኙና አረመኔዉ የወያኔ ጦር በኦሮሞ ሀዝብ ላይ የሚፈጽመዉን ፋሽስታዊ የግዲያ ኣድማሱን በማስፋት ዛሬ በንጹሃን ዜጎች ላይ በፈጸመዉ መጠነ ሰፊ ጭፍጨፋ በደቡባዊ የኦሮሚያ ክፍል ሞያሌ ዉስጥ በርካታ ዜጎች ላይ በተወስደ የጭካኔ አርምጃ በርካታ ዜጎች ለህልፈት ሲዳረጉ ብዙዎች ከፍተኛ የኣካል ጉዳት እንደደረሰባቸዉ ለማወቅ ተችሏል።
የሟቾች ቁጥር  እስካሁን የኣስራ ሶስት መድረሱ ሲታወቅ ከነዝያ መሃል ኣስከሬናቸዉ በሆስፒታል የሚገኘዉ የስምንት ስው ስም ይፋ ሆኗል
1.ተማም ነጌሶ የትምህርት ቤት ዳይረክቴር
2.ኤርሚያስ በዳኔ የሬስቶራንት ሰራተኛ
3.ካኑ ገሮ
4.ጎሎ
5.ሚሃመድ ኡርጌ
6.ካኑ ቃንጫሮ
7.መሃመድ ካምጴ
8.ታሪ ሻማ
ሲሆኑ ኣራት የሟቾች ኣስከሬን በወታደሮች ወደ ካምፕ ተወስዷል። ይህን በህዝብ ላይ የተፈጸመ ኣሳዛኝ ጨፍጨፋና የጉዳቱን መጠን እየተከታተልን እናቀርባለን።
Filed in: Amharic