
• የኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ባለፈው ታኅሳስ ወር. ግምገማ አካሂዶ ነበር።
• በግምገማው 4ቱ ድርጅቶች በተናጥል ምን ማድረግ እንዳለባቸው ውሳኔ አሳልፏል።
• በአሁኑ ስብሰባ ድርጅቶቹ ውሳኔውን ከምን እንዳደረሱት ይገመግማል።
• በግምገማው ከተስማማ ለኢህአዴግ ሊቀመበርና ጠ/ሚ እጩዎች ላይ ይነጋገራል።
• ለምክር ቤቱ እሚቀርቡ 3 እጩ ጠ/ምኒስትሮች ላይም ይመካከራል።
• በቀጣዩ 180 አባላት ያሉት የኢህአዴግ ምክር ቤት ስብሰባ ይጠራል።
• ከምክር ቤቱ ከግማሽ በላይ ከተገኙ ምዕላተ ጉባኤው የተሟላ ይሆናል።
• ምክር ቤቱ የኢህአዴግ ሊቀመንበርን ይመርጣል።
• ከ180ዎቹ ቢያንስ 60 ድምጽ ያገኘ አባል የጠ/ምኒስትር እጩ ሆኖ ይቀርባል።
• ም/ቤቱ በጠ/ሚር እጩዎች ካልተስማማ የራሱን እጩዎች ሊጠቁም ይችላል።
• አሸናፊ ሆኖ የወጣው ግለሰብ ለፓርላማው ቀርቦ ጠ/ምኒስትር ይባላል።
• ጠ/ሚ/ር ሌላ የኢህአዴግ ሊቀመንበር ደግሞ ሌላ ሰው ሊሆንም ላይሆንም ይችላል።
ስለዚህ የአቶ ኃይለማርያምን ራዕይ እሚያስፈጽመውና ህዝባዊ አመጹን ቀጥ ለጥ ሊያደርግ በሚችለው ቀጣዩ ጠቅላይ ምኒስትር ማንነት ህዝቡ ይገረማል። የኢትዮጵያም ህዝብ እስከዛሬ ድረስ በታሪኩ አይቶ እያማያውቀው በመሆኑ ትልቅ “ሰርፕራይዝ” ሊሆን መቻሉ ፍንጭ እየተሰጠን ነው። ቀላጤዎቻቸውም በእስካዛሬው ግምታችን ውድቅ መሆን ከወዲሁ እየተደሰቱ ይመስላል። እኛማ ወግ ደርሶን ይሄ ቢሆን ያ ቢሆን ማለታችን፣ መቸም ያው ከምናምንቴያቸው አይወጡም ለማለት እንጂ የሌላቸውን ደህና ሰው አምጠው ይወልዳሉ ብለን አልሰጋንም። እኛማ በትንቢታችን ማንንም ብታመጡም አታመልጡም እያልን ነው። ይልቅ ሰው እንጂ ጊዜ መግደል እማታውቁ አስቸኳዮች ሆናችሁ ምን ያንቀረፍፋችኋል?! ያው እንደ ሕጻን ልታሞኙን ስለሚያምራችሁ አሻንጉሊታችሁን ስጡንና እንጫወትበት። ለሰቆቃው ፋታ ይሰጠን ይሆናል እያልን ነው!