በፍቃዱ አባይ
ለተወዳጁ አርቲስት ፍቃዱ ተ/ማርያም የህክምና ርዳታ ትብብር እንዲደረግ ተጠየቀ።

በዚህም መሰረት ለአርቲስት ፍቃዱ ተ/ማርያም የኩላሊት ልገሳ የሚያደርጉ ስዎች እንደሚያስፈልጉት አንዲሁም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አጎዛ ቅርንጫፍ የባንክ ቁጥር 1000239345488 በአርቲስት መሰረት መብራቴ፣በአርቲስት መቅደስ ጸጋዬ እንዲሁም በአቶ ሳምሶን ብርሀኔ ስም ጊዜአዊ አካውንት ተከፍቷል።
አንዲሁም በውጭ አገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በGoogle.Go Fund me. please help save Fekadu. ላይ የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ እንደሚቻል ተነግሮአል።ሰዎችም ከተሰጡት አካውንቶች ውጭ በመሰል መልኩ ሊከፈቱ ከሚችሉ አሳሳች መረጃዎች እንዲጠነቀቅም ምክር ተላልፏል።ጊዜአዊ ኮሚቴው 7 የጥበብ ባለሙያዎች እና በጎ ፈቃደኞች እያስተባበሩት ይገኛል።በጋዜጣዊ መገለጫው ላይ ከመገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች በተጨማሪም የአርቲስት ፍቃዱ ተ/ማርያም የስራ ባልደረቦች ታድመዋል።ለፍቃዱ ተ/ማርያም የኩላሊት ልገሳ ለማድረግ ለሚፈልጉ +251 911 86 43 96 ወይም +251 913 02 34 44 በመደወል መረጃዎችን ለማግኘት እንደሚቻልም ተነግሮአል።የፍቃዱ ተ/ማርያም የደም አይነቱ A ሲሆን የኩላሊት ልገሳ ለማድረግ የሚችሉ ስዎች A ወይም O የደም አይነት ያላቸው ስዎች ናቸው።