♦የሞተውና ቁስለኛው ከሃምሳ በላይ ነው!
♦ብዛት ያለው ከብሬን እስከ ክላሽን መሳሪያ ተማርኳል!
ሰሜን ጎንደር
ማክሰኞ መጋቢት 11 2010

የወያኔ ሰራዊት በመላው አማራ በተለይ ሰሜን ጎንደር ላይ ትጥቅ ለማስፈታት እያደረገ ያለው ሙከራ ከባድ ዋጋ እያስከፈለው ይገኛል። የወያኔን ተንኮል ቀድሞ የተረዳው መሳሪያ ታጣቂ ገበሬ በየጎበዝ አለቃው ተደራጅቶ ጠላትን እየቀጣው ነው። በዚህ ሰሞን ሮቢት አርማጭሆ የተመዘገበውን ድል ማስታወስ በቂ ነው። ጥሪቱን አሟጦ የገዛውን የድንበር መጠበቂያና የህልውና ዋስትናውን መሳሪያህን አውርድ የተባለው ህዝብ በወያኔ የእብሪት ድርጊት እልህና ቁጭት ውስጥ ገብቶ በሙሉ ወኔ ገጥሟል። ከበርሃው ጀግኖች የመጣው መልእክት ህዝባችን ከጎናችን አይለየን የተቃጣብንን ጦርነት አክሽፈን እናሸንፋለን ብለዋል።
እግዚአብሔር ለተገፉ ሃይልና ድልን ይሰጣል!
ድል የህዝብ ነው!
ሙሉነህ ዮሃንስ