ሌሎች በጠላትነት ተፈርጀው፣ ሲሰደዱ፣ ሲታሰሩና ሲገደሉበት እሳቸው እንደፈለጋቸው እየተናገሩና እንደፈለጋቸው እንዲነግዱ እንደ እንቁላል እሚጠበቁት ጀኔራል ፃድቃን የሰጡት አሰተያያት አሁን ተፈጻሚ እሚሆን ይመስላል እየተባለ ነው። ጀኔራል ሳሞራ ተነስተው ብርሃኑ ኤታማዦር ሹም እንዲሆኑ ታጭተዋል። ጌታቸው አሰፋን በማንሳት ወርቅነህ ገበየሁን ደህንነት ሹም ለማድረግ በወርቅነህ ፋንታ ደግሞ ተሾመ ቶጋን ለውጭ ጉዳይ በማጨት ዝርዝርና ክርክር እየተካሄደ መሆኑም እየተሰማ ነው። ጻድቃን ምንም እንኳ ሰዓረ የተሻሉ ቢሆኑም ብሄር አመጣጥኖ የተሳሳተ ግንዛቤ እንዲቀር ብርሃኑን ማድረጉ ጠቃሚ ነው ሲሉ ባንድ ሰው ቦታ መለዋወጥ የአገር ግንዛቤ ይስተካከላል ብለው ማሰባቸው ምንኛ ንቀት አላቸው ብሎ ማሰብ ይቻላል። ከአንድ ጎሳ የተቀዳውን ያን ሁሉ ጀኔራልና የአዛዦች መንጋ የተሳሳተ ግንዛቤ ብቻ ብሎ ማቅለሉም ልክ አይደለም። እንደዚያ ያለ ንቀትና ድርቅና ላይ መግባባት ከሌለ ለሳሞራ የመጣው ቁጣ ለጻድቃንም መትረፉ አይቀርም ። ጨዋታው ሠራዊቱ ውስጡን እንዲቀይር በሚፈለጉ እና ሠራዊቱ ራሱ እንዲቀየር በሚፈልጉ መካከል መሆኑ አልገባቸውም። ለውጥ በሚናድ ቡድን ጭምር እንጂ በሚቀየር ሰው ብቻ አይመጣም መባሉም ለዚህ ነው። ዛሬ ነቅሎ የወጣው የአምቦ ህዝብ አብይን ደግፎ ሳይሆን ህወሓትንም ነቅፎ ነው። የተሳሳተ ግንዛቤ ስላለው ብቻ ሳይሆን የቡድን አገዛዝ ሊያበቃ መንገድ የተያዘም መስሎት ነው።
ለጻድቃን ይተርፋል (ደረጀ ደስታ)
Filed in: Amharic