>
5:13 pm - Thursday April 18, 2030

ዳንጎቴና ሞሶቦ!?! በአንድ ድንጋይ ሶስት ወፍ!?! (ጌታቸው ሽፈራው)

ሙገር ሲሚንቶ  ለበርካታ አመታት ኢትዮጵያ ውስጥ የሲሚንቶ ገበያውን ተቆጣጥሮ ኖሯል። በመሃል ግን ትህነግ/ህወሓት ሞሶቦን አቋቋመ። በቢሮክራሲው፣ የሰው ሀይሉን በመንጠቅ፣ በአሻጥር ሙገርን ባዶ አደረገው። አከሰረው። ሆን ተብሎ ሲሚንቶ እንዲጠፋ ተደረገ። የትህነግ/ህወሓት ሞሶቦ በእጥፍ እጥፍ ሸጠ።
የሲሚንቶ  ገበያው ሲደራ የውጭ ኩባንያውም ገባበት።  ዳንጎቴ በምሳሌነት ይጠቀሳል። የዳንጎቴን  ሰራተኛ ሞሶቦ ሙገር ላይ እንዳደረገው በተወሰነ ብር አባብሎ መንጠቅ አይችልም። በማስፈራራት፣ በሴራ እንደ ሙገር ለማንበርከክ አይጥሩም። የውጭ ኢንቨስትመንት የሚሉትን መና ያስቀራል። በዳንጎቴና በሞሶቦ መካከል ያለው ጥራት የትየለሌ ነው። ሞሶቦ ገበያውን ለዳንጎቶ እየለቀቀ መጣ! በዚህ ከቀጠለ መክሰሩ ነው! አፈር አፍሶ የሚሸጠው ሞሶቦ ከከስ ደግሞ ኢፈርት ከሰረ ማለት ነው። ፖለቲካውን በገንዘብ ኃይል የተቆጣጠረው ትህነግ ከሰረ ማለት ነው!
ትናንት ምን ተፈጠረ? ኃላፊውና ሌሎች ግለሰቦች ተገደሉ።
ምን አልባትም ኢትዮጵያ ለመዋለ ንዋይ ምቹ አይደለችም፣ የአደጋ ዞን ነች ብለው ጥለው  እንዲሄዱ ይሆናል። ይህ የተደረገው ደግሞ ኦሮሚያ  ላይ፣ ያውም በአብይ ዘመን። ለትህነግ/ህወሓት ብዙ ትርፍ ያለው ሴራ ይመስለኛል።
Filed in: Amharic