ለብዙ ግዚያትም ሰው መሆናችንን እንድንጠላ አድርጎናል::ይሄ ሁሉ ዘግናኝ ጭፍጨፋ የተፈፀመው በኢህአዴግ ባለስልጣንና በኦኖጎቹ የያኔው የማስታወቂያ ሚ/ር በነበሩት ዶ/ር ዲማ ነገዎና ሌንጮ ለታ ጭምር ነው::
ኦነግ በጠረባ ተመትቶ 50 ሽህ ጦሩን በትኖ ከሀገር ሲፈረጥጥ የአማራውን ጭፍጨፋ በሚመለከት ኢህአዴጎች ጭፍጨፋውን ያካሄደው ኦነግ ነው ምክኒያቱ ደግሞ በሚኒሊክ ግዜ ደረሰብን ላለው በደል የበቀል ጅራፍ ነው ሲል:ኦነግ ደግሞ ጭፍጨፋውን ያካሄደው ኢህአዴግ በተለይም ህወሀቶች በህዝቦች መካከል ደም ለማቃባት ስለፈለጉ ያደረጉት ነው በማለት ለተለያየ ሚድያ ሲገልፁ ኖረዋል::
ሜዳውም ፈረሱም ይሄው እንዳለው ያገሬ ሰው አሁን እርስ በራሳቸው ሲካሰሱ የነበሩት ሰዎች(ኢህአዴግና ኦነግ)ሸገር ላይ ይገኛሉ:: አሁንስ በበደኖና በአርባጉጉ የዘር ጭፍጨፋ የፈፀመው ማን ነው?