ቬሮኒካ መላኩ
ጠቅላይ ሚኒስትሩም ለራሱ ዋስትና የሚሆነው ህጉ እንጅ ቡድኖች አይደሉም።ጠ/ሚ ዶ/ር አቢይ አህመድ አዲስአበባ የተቋቋመችበትን ቻርተርና ህግ በቡልዶዘር ጠርምሶ ህጉን በቀይ እስኪብርቶ እየሰረዘ ነገ በቴሌቪዥን መጥቶ እኔን “ህግ ይከበር ፣ ህግ አክብሪ! !” የማለት የሞራል ብቃት የለውም።
…
ወይም ለይቶለት እንደ ፊውዳል ዘመን የአውሮፓ ነገስታት እንደ እነ ንጉስ ሊዊ ዶ/ር አቢይም በይፋ ወጥቶ ከዛሬ ጀምሮ “I am the constitution “, ” I am the Charter!” ,” I am the law !” ይበለንና ቁርጡን አውቀን ፊናችንን እንለይ ።
በተረፈ ህግ የሚጥሱትን በህግ እንጠይቃለን ፣ሌባን እናስራለን” እየተባለ አዲስ አበባ መመስረቻ ህግ ሲጣስ የአዲስ አበባ ቁልፍ ሲሰረቅ ዝም ማለት የመርህ ሰው አለመሆን ነው።
…
እነ ማንደላን እያደነቁ ፣ እነ መሀተመ ጋንድን እያወደሱ ፣ ስለ እነ ሶቅራጥስ የሞራል ልእልና ለአርቲስቶች እየሰበኩ በጎን ተቃራኒውን ሆኖ መገኘት ስሁት ነው ።
…
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚያደንቀው አርቲስቶችን ሰብስቦ ስሙን ሲጠቅሰው የነበረው ሶቅራጥስ በገዥዎች ታስሮ የሞት ፍርዱን በሚጠባበቅበት እስር ቤት ውስጥ እያለ ተማሪዎቹ እስር ቤቱን ሰብረው ገብተው ” ና ውጣ! ከሞት ተርፈሃል ፣ ከአቴንስ የምትወጣበትንም ጀልባ አዘጋጅተናል ” ሲሉት ምን አለ?
…
ሶቅራጥስ እንደዚህ አለ… ” በግሪክ ህግ ተወልጄ ፣ በግሪክ ህግ ልደቴን አክብሬ ፣ በግሪክ ህግ አግብቼ ፣ የግሪክን ህግ ተቀብዬ ኖሬ በግሪክ ህግ ሞት ሲፈረድብኝ ለማምለጥ ከሞከርኩ ምኑን ሶቅራጥስ ሆንኩኝ? ” በማለት ከእስር የማምለጥ ሙሉ አቅም እያለው እኔ ኖሬ ውሸት፣ ህግ አልባነት ከሚነግስ እኔ ሞቼ እውነት ትሩር ፣ብሎ በግሪክ ህግ የተፈረደበትን የሄሞሎክ መርዙን ጠጥቶ እና እያሰበ ወደ ዘላለም ዝምታ ነጎደ .።
…
ህግ ካላከበርን ፤ ፍትህና እና እውነት ካልተከበሩ ለዘረኝነት ዘረኝነትማ መለስ ዜናዊ አልነበረም እንዴ?!
አሁንም እንደቃልህ ሆነህ ህግን እስክታከብርና ወደ ትራክህ እስክትመለስ እየጠበቅንህ ነው።
