>

ኢህአዴግን ስሙን ከምንቀይረው ግብሩን እንቀይረው!!!  (ዶ/ር ዐቢይ አህመድ) 

ኢህአዴግን ስሙን ከምንቀይረው ግብሩን እንቀይረው!!!
 ዶ/ር ዐቢይ አህመድ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በሎሳንጀለስ ከዳያስፖራ ማህበረሰብ ጋር  ሲወያዩ ከተናገሩት ዋና ዋና ነጥቦች:-
ልሰርቅ ስደራደር፣ ስጠጣና  ስቅም ሞቼ አታገኙኝም፤ ለአገር እየሰራሁ ለአገር እየተጋሁ  ምንም ዓይነት ሞት ቢመጣ  ክብር አድርጌ ነው የምወስደው፡፡
 የደህንነት ፍልስፍናው ጠባቂ ህዝብ የሚለው ነው፡፡
 ሪፎርመርን እንጂ ሪፎርምን መግደል አይቻልም፤ ያ ቢቻል ኖሮ ኬኔዲ ሲሞት ጆንሰን ተነስቶ ተዓምር ባልሰራ ነበር፡፡
 ኢትዮጵያዊነት አሁንም ሱስ ነው፤ ኢትዮጵያዊነት ሱስ ነው ያሉት ፈላስፋ በየቀኑ ስራቸው ኢትዮጵያዊነት ሱስ መሆኑን ያረጋገጡ ምርጥ መሪ መሆናቸውን ላረጋግጥላችሁ እፈልጋለሁ፡፡
 ብዙ ጊዜ ራሳችንን ማዕከል እያደረግን እንጂ ሌሎችን  በሚያቅፍ መንገድ ማቀድ ስለማናስብ  ብዙ የጎደለ ነገር አለ፣ ከተባበርን ግን ይሟላል ብዬ አምናለሁ፡፡
 በእንደዚህ ዓይነት በዓላት ኤርትራውያን ወንድሞቻችና እህቶቻችን አብረውን እንዲሆኑ ልባችንን ከፍተን መቀበል ነው፤ እውነት ለመናገር ኤርትራውያን ፍጹም ፍቅር የተሞላባቸው ናቸው፣ ኤርትራውያን እና ኢትዮጵያውያን ምናችንም አይለያይም፣ የኢትዮጵያ ኮሚዩኒቲ ከምትሉ ኢትዮጵያ- ኤርትራ ብላችሁ Positive energy ካመነጫችሁ እዚያ ያለውም ይቀየራል፡፡
 የኢሕአዴግ ስም መቀየርን በተመለከተ፣ ስምን የሚቀይርና በግብር እዚያው የሆነ ኢሕአዴግ ከሚሆን ግብሩን የሚቀይርና ግብሩ ስሙን የሚቀይር ኢሕአዴግ ይሁን፤ አስቀድመን ስም ቀይረን በግብር እዚያው ከሆንን ያው ኪሳራ ነው፡፡
 ሰውን  መግደል ሽንፈት ነው፣ ሰው መግደል ውድቀት ነው፣ ሰው የሚገድል ሰው አይደለም፣ የምንገዳደል ሳይሆን የምንተቃቀፍ መሆን አለብን፡፡
 ጥያቄ ስንጠይቅ የእኔ ብለን የምንጠይቅ ከሆነ መልሱ ይራዘማል፣ የእኛ ጥያቄ ጠይቀን መልሱን እኛው እንመልሰው፡፡
Filed in: Amharic