“ለውጡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል ውጤት ነው” አቶ ዳዉድ ኢብሳ
..
በአሁን ወቅት እየታየ ያለው ለውጥ በሕዝብ ትግልና መስዋዕትነት የተገኘ ነው ሲሉ የኦነግ ሊቀ መንበር አቶ ዳዉድ ኢብሳ አዲስ አበባ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በሰጡት መግለጫ ተናገሩ::
አቶ ዳዉድ እንዳሉት ግንባራቸው ከ26 ዓመታት በሗላ ወደ ኢትዮጵያ የተመለሰው መንግሥት ባደረገው ጥሪ በሰላማዊው የፖለቲካ መድረክ ላይ ለመሳተፍና በሃገሪቱ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲጠናከር እንደሚሰሩ ተናግረዋል::
በቀጣይ ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ለማድርግ ከመንግሥት: ከአባሎቻቸው: ከደጋፊዎችና ከተቃዋሚ ድርጅቶች ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ ገልፀዋል::
በረጅም ጊዜም በመላው ሃገሪቱ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲሰፍንና ሕዝቡም በሁሉም ደረጃ በምርጫ መሪዎቹን ለመምረጥ የሚያስችል ሥርዓት በመገንባት እንደሚሳተፉ ተናግረዋል::
በሃገሪቱ የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን በመስራት በኩልም ኦነግ አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርግ አቶ ዳዉድ ገልፀዋል::
የኦሮሞ ነጻነት ግምባር አመራሮች በመስቀል አደባባይ በርካታ ሺህ ህዝብ በተገኘበት ደማቅ የአቀባበል ስነስርአት ተደርጎላቸዋል።
https://www.youtube.com/watch?v=e87JuXQgJ9w
