>

እየተገነባ ያለዉ የአብይ አህመድ አምባገነንነትና አማራ አግላይ ስርዓት !!! (ደሳለኝ ጫኔ ዳኘው)

እየተገነባ ያለዉ የአብይ አህመድ አምባገነንነትና አማራ አግላይ ስርዓት !!!
ደሳለኝ ጫኔ ዳኘው
ከታች ከተጠቀሱት 9 ወሳኝ ቦታዎች መካከል ኦዴፓ 5 ፣ ደኢህዴን 2 ፣ ህወሃት 1 ፣ አብዴፓ 1 ፣ ኢሶዶፓ 1 ሲያገኙ ፣ የኛዉ ጉድ አዴፓ በብላሽ ባዶዉን መዉጣቱ የትላንቱ ብአዴን የዛሬዉ አዴፓ ከተላላኪነትና ከአጋፋሪነት ያለፈ ድርሻን መወጣት የማይችል መሆኑን እንረዳለ!!!
አብይ አህመድና ከመጋረጃ ጀርባ የመሸጉት ስትራቴጂስቶቹ በደንብ የተጠና ፣ ስልታዊ ፣ በመደመር ሰበብ አዴፓን በመሸንገል የተተገበረ የፓለቲካ ጨዋታ በድል ጀምረዋል፡፡ የፌደራል ወሳኝ ሚኒስትር መስሪያቤቶችን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በኦሮሞ የመዉረርና የመቆጣጠር ፕሮዢ ለአማራዉ ህዝብ አይን ያወጣ ክህደትና ሸፍጥ ነዉ፡፡ ህዝባችን በአዴፓ ላይ ለሁለት ሳምንት ጥሎት የነበረዉን “ሊለወጡ ይሆን” ተስፋ ጊዜ ሳያባክን ስህተት መሆኑን ያሳየ ማኪያቬሊዊ ክስተት ነዉ፡፡ የአማራ ህዝብ አዲሱን የአብይ አህመድ ካቢኔ በምንም መልኩ እዉቅና የማይሰጠዉ ሲሆን ፤ ይህ አይን ያወጣ ሸፍጥ ግን በረከተ መርገምት ይዞልን እንደመጣ ግልጽ ነዉ፡፡ ባለጭምብሉ አብይ ጭምብሉን አዉልቆ ጥሎ በትክክለኛ ማንነቱ የተገለጸ ሲሆን ፤ ህዝባችን ለወራትም ቢሆን የማይጨበጥ ተስፋ በማድረጉ ጥቂት ሲጎትተን ነበር፡፡ ዛሬ ላይ ሆነን ግን “እኩል የጾታ ስብጥር” ካቢኔ በማዋቀር ስም በመሰራት ላይ ያለዉን የአብይ አህመድን ጭልጥ ያለ አምባገነንነት አይተንበታል፡፡ 
 
ደመቀን በተቀነባበረ መንገድ በወታደር የደሞዝና ጥቅማጥቅም ጥያቄ ሰበብ በማስወገድ ቤተ-መንግስቱን ብቻዉን መያዝሞክሮ ከሸፈበት እየተባለ የሚታማዉ አብይ ፣ ዛሬ ደግሞ ቁልፍ ሚኒስትሪዎችንና በስራቸዉ ያሉ ተጠሪ መስሪያቤቶችን አዲስ ሹመትና አወቃቀር በማየት ብቻ አማራን ከወሳኝ የዲፕሎማሲ ፣ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ፣ ፀጥታ ፣ መከላከያና ደህንነት ተቋማት ሙሉ በሙሉ ያገለለ እንደሆነ ለመረዳት አብይም ሆነ ነብይ መሆንን አይጠይቅም፡፡  ዳግማዊትን የመሰለች ብቁ የአዲስ አበባ አማራ የአዴፓ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ሆና በመመረጧ ኦዴፓና አብይ ደስተኛ አልነበሩም፡፡ ህጋዊ ከንቲባነቱ ለዳግማዊት ይገባል የሚለዉ ጥያቄ እንዳይነሳ ፣ ለአክራሪዉ ታከለ ኡማ የስልጣን ተፎካካሪ እንዳይፈጠር ፣ አማራም በአዲስ አበባ አስተዳድር ድርሻ እንዳይኖረዉ ዳግማዊትን ገሸሽ በማድረግ በሙስናና ብልሹ አሰራር የተጨማለቀዉን ታርጋ ለጣፊ መስሪያ ቤት እንድትመራ ሹመት ሰጠሁ ብሏል፡፡ 
 
የአብይንና የኦዴፓን ቅጥ ያጣ የስልጣን  ጠቅላይነት ጥም ፣ የአዴፓ የአማርኛ ቋንቋ ምሩቃንን ሚኒስትር በማድረግ ለአማራ ህዝብ ያስተላለፈዉ የሾርኔ መልዕክት ፣ ትምህርት ሚኒስቴርን ከሁለት ከፍሎ ለአማራ ማካፈሉ በራሳቸዉ የሚናገሩት ብዙ መልዕክት ነዉ፡፡ አብይ በሚኒስትሮች ምክር ቤት በመገዳደር የአማራን ህዝብ ጥያቄ ያነሳሉ ብሎ ያሰባቸዉን እንደ አምባቸዉ መኮንናና መላኩ አለበል አይነት አማራዎችንም ከካቢኔዉ አስወግዷል፡፡ የተሾሙ አማራዎችም ብዙዎች ለአዴፓ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት እንኳ ያልተመረጡ ዝቅተኛ ፕሮፋይል ያላቸዉ የአዴፓ አባላት መሆናቸዉ አብይ ለአማራ ያለዉን ንቀትና ጥላቻ በይፋ የሚያሳይ ነዉ፡፡ 
 
ዳግማዊትን ጨምሮ ዶ/ር ሂሩትን የመሰሉ በህዝባችን ዘንድ በበጎ የሚታዩ የአማራ ልጆች ይህን ሸፍጥ በመቃወም አዲሱን ስልጣናቸዉን መልቀቅና የአብይ አህመድን አምባገነንነት በይፋ በመቃወም ከህዝባቸዉ ጋር ካልቆሙ ነገ እነርሱን አያርገኝ፡፡ አምባቸዉም እየተወራ ያለዉን የእንግዳ ተቀባይነቱን ስልጣን ከተቀበለ የፓለቲካ ሞት ለመሞት እንደተዘጋጀም በዚህ አጋጣሚ ይታወቅ፡፡ ከዚህ በኋላ ይህን ሸፍጥ ተቀብሎ አዴፓ ከአብዩ ኦዴፓ ጋር ከቀጠለ የአማራ ህዝብ መቸ ምን ማድረግ እንዳለበት ያዉቃል፡፡ የህወኃትን ቅልጥም ሰብሮ ለልምሻ የዳረገዉ ህዝባችን ክብሩን አዋርደዉ ሊገዙት ለመጡ አምባገነኖች ያደረገዉን ከፍሽስቶቹ ሞሶሎኒና የአገርቤት ተላላኪዎቹ የማይማር ለተመሳሳይ ስህተት መዳረጉ አይቀርም፡፡
 
ኦዴፓ አዴፓን እንደ ስትራቴጅካዊ አጋር ሳይሆን ስልጣኑን የማደላደያ ታክቲካል አጋር አድርጎ ከተጠቀመበት በኋላ ከፌደራል ስልጣን በጠረባ መትቶ አባሮታል፡፡ ከታች ከተጠቀሱት 9 ወሳኝ ቦታዎች መካከል ኦዴፓ 5 ፣ ደኢህዴን 2 ፣ ህወሃት 1 ፣ አብዴፓ 1 ፣ ኢሶዶፓ 1 ሲያገኙ ፣ የኛዉ ጉድ አዴፓ በብላሽ ባዶዉን መዉጣቱ የትላንቱ ብአዴን የዛሬዉ አዴፓ ከተላላኪነትና ከአጋፋሪነት ያለፈ ድርሻን መወጣት የማይችል ፣ ለአማራ ህዝብ የዉርደትና የሃፍረት ምንጭ ከመሆን መዝለል የማይችል ድርጅት እንደሆነ እንረዳለን፡፡ 
 
1. የሰላም ሚኒስቴር ተጠሪ የሆኑ አስፈፃሚ ተቋማት ዝርዝር
 
i. የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት
ii. የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ
iii. የፋይናንስ ደህንነት መረጃ ማዕከል
iv. የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን
v. የኢሚግሬሽን፣ ዜግነትና ወሳኝ ኩነቶች ኤጀንሲ
vi. የስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ ኤጀንሲ
vii. የብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን
viii. የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ስትራቴጂክ ጥናት ኢንስቲትዩት ናቸው።
 
2. የአገር መከላከያ ሚኒስቴር ተጠሪ የሆኑ አስፈፃሚ ተቋማት ዝርዝር
 
i. የሀገር መከላከያ ኢንጂነሪንግ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ
ii. ጋፋት አርማመንት
iii. ሆሚቾ አሙኒሽን ኢንጂነሪንግ
iv. ደጀን አቪየሽን ኢንጂነሪንግ
v. ብራና ማተሚያ ድርጅት
vi. የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ
vii. የመከላከያ ኮንስትራክሽን ዲዛይን ድርጅት
viii. የመከላከያ ኮንስትራክሽን ዕቃዎች ማምረቻ ድርጅት ናቸው።
 
3. ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተጠሪ የሆኑ አስፈፃሚ ተቋማት ዝርዝር
 
i. የውጭ ግንኙነት አገልግሎት ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት
ii. የዲያስፖራ ኤጀንሲ ናቸው።
 
4. ለገንዘብ ሚኒስቴር ተጠሪ የሆኑ አስፈፃሚ ተቋማት ዝርዝር
 
i. የመንግስት የልማት ድርጅቶች የዞታና አስተዳደር ኤጀንሲ
ii. የኢትዮጵያ ሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ
iii. የመንግስት ግዢና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ
iv. የመንግስት ግዢና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ናቸው።
 
5. ለጠቅላይ ዓቃቤ ህግ ተጠሪ የሆኑ አስፈፃሚ ተቋማት ዝርዝር
 
i. የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበራት ኤጀንሲ
ii. የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ጽ/ቤት
iii. የፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር 
iv. የፍትህና የሕግ ምርምርና ስልጠና ኢንስቲትዩት
v. የሠነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ ኤጀንሲ
vi. የፌደራል ግብር ይግባኝ ሰሚ ጉባኤ ናቸው።
 
6. ለንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ተጠሪ የሆኑ አስፈፃሚ ተቋማት ዝርዝር
 
i. የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት
ii. የቆዳ ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት
iii. የብረታ ብረት ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት
iv. የምግብ፣ የመጠጥና የፋርማሲቲካል ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት
v. የኬሚካልና የኮንስትራክሽን ግብዓቶች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት
vi. የስጋና ወተት ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት
vii. የፌዴራል አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች ማስፋፊያ ባለስልጣን
viii. የንግድ ውድድርና ሸማቾች ጥበቃ ባለስልጣን
ix. የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለስልጣን
x. የኢትዮጵያ ብሔራዊ አክሬዲቴሽን ጽ/ቤት
xi. የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኤጀንሲ
xii. የኢትዮጵያ ብሔራዊ የስነ-ልክ ኢንስቲትዩት
xiii. የኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ኤጀንሲ
xiv. የኢንዱስትሪ ግብዓት አቅራቢ ልማት ድርጅት ናቸው።
 
7. ለገቢዎች ሚኒስቴር ተጠሪ የሆኑ አስፈፃሚ ተቋማት ዝርዝር
 
i. የጉምሩክ ኮሚሽን
ii. የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ናቸው።
 
8. ለፕላንና ልማት ኮሚሽን ተጠሪ የሆኑ አስፈፃሚ ተቋማት ዝርዝር
 
i. ማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ
ii. የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ናቸው።
 
9. ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጠሪ የሆኑ አስፈፃሚ ተቋማት ዝርዝር
 
i. የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን
ii. የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
iii. የአካባቢ፣ ደንና አየር ንብረት ለውጥ ኮሚሽን
iv. የሥራ ዕድል ፈጠራ ኮሚሽን
v. የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ
vi. ቱሪዝም ኢትዮጵያ
vii. የቤተ መንግስት አስተዳደር ናቸው።
 
አዴፓ ይህን ሹመት ተቃዉሞ በይፋ መግለጫ ካልሰጠና ከኢህዴግ እንደሚወጣ አስጠንቅቆ ባስቸኳይ የካቢኔ ማሻሻያ እንዲያደርግ ኦዴፓን ካላስገደደ የአማራን ህዝብ ጥቅም የማስጠበቅ ፍላጎት ፣ አቅምና ቁርጠኝነት እንደሌለዉ ቆጥረን የህዝባችን ጥቅም ፣ ፍላጎትና ክብር ያሚያስጠብቅ ትግል በማድረግ የአማራን ህዝብ ዳግም ዉርደትና አንገት የማስደፋት ሙከራ እናከሽፈዋለን፡፡
 
አማራ በልጆቹ ትግል ታሪኩን ያድሳል!
Filed in: Amharic