>

የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች ነገ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ!

Befikaduበነገው ዕለት የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች ማኅሌት ፋንታሁን፣ አቤል ዋበላ እና በፍቃዱ ኃይሉ በአራዳ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ።በነገው ዕለት ከሚቀርቡት ሶስቱ ጦማሪዎች ውስጥ ኣንዱ የሆነው ጦማሪ በፈቃዱ ሃይሉ (ፎቶ) በፖሊስ ለተቀነባበረው ባለ30 ገጽ የውሸት ዶክመንት ላይ  እንዲፈርም  17 ቀናት  በጨለማ ቤት ውስጥ ቆይቶ ነበር። ቶርቸርም ተደርጎኣል።ባለፈው ጊዜ ለይስሙላው ፍርድ ቤት በፖሊሶች ተጽዕኖ እየተደረገበት መሆኑን  ባገኛት  ደቂቃ  በኣንደበቱ  መተንፈሱም  ኣይዘነጋም።

በንጹሃን ላይ ወንጀሎችን በመፈብረክና ብሎም ዜጎቹን በማሰርና በማሰቃየት የሚረካው ወያኔን ጠንቅቆ የሚያውቀው ወጣቱ ጦማሪ በፍቃዱ ሃይሉ ይሄ ሁሉ ግፍ ይፈጸምበት እንጂ፣ የወያኔን የፍትህና የህግ ሂደት ከመታሰሩ ቀደም ብሎ በማህበራዊ ድረ -ገጾች ላይ  የጦመረው  በዚህ መልኩ ነበር  ‘‘ወደፊት የሚደርስብኝን ግፍም ሆነ እስር ኣልፈራም።  በምታስርበት ጊዜ ከሚፈበረክብኝ ክስ ራሴን መከላከል ያለመቻሌን ሳስበው ግን ያስፈራኛል። ነበር ያለው። 

የህብረተሰቡ ብሶት ብሶታችን ነው ”ስለሚያገባን እንጦምራለን” ያሉት ጦማሪዎች በጡንቸኞች እጅ ከወደቁ 79 ቀናቶች ኣልፎኣቸዋል። በነገው ዕለት ማኅሌት ፋንታሁን፣ አቤል ዋበላ እና በፍቃዱ  ኃይሉ በአራዳ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት የሚቀርቡ ስለሆነ ኣጋርነታችሁን እንድታሳዩዋቸው ዞን ዘጠኞች ኣሳስበዋል። እኛም የምንለው  ኣጋርነትዎን በማሳየት የሞራል ስንቅ ይሁኗቸው ነው።

Filed in: Amharic