>

ዶ/ር አብይን በእውቀት እንወቅ (ዶ/ር ዘላለም እሸቴ)

ዶ/ር አብይን በእውቀት እንወቅ

ዶ/ር ዘላለም እሸቴ

የኢትዮጵያ ነገር መላ እንደሌለው፤
አምላኳ አወቀላት ጉዳዩ ሌላ ነው።

ብርሃን ፈነጠቀ ዶ/ር አብይ መጣ፥
ኢትዮጵያን ሊታደግ እርሱ እንቅልፍ አጣ፥
ሁሉም ደገፈና አንድ ላይ ሰልፍ ወጣ፥
ልናርፍ ነው ብሎ ከነበረን ጣጣ።

ቃሉ የሚጣፍጥ የሌለው ወደር፥
ትህትናው ግሩም ልዩ ከምድር፤
ፅናቱ የሚገርም ደግሞም እይታው፥
ድፍረቱ ትጋቱ እጅግ የሚደንቀው።

ጠላቱ እያደር እየበዛ ሲሄድ፥
ወደድኩህ ያለውም ሊያወጣው ከመንገድ፤
ከወዲህ ከወዲያ ሁሉም ሲጎትተው፥
ስምም እያወጣ ቢጎነታትለው፤
ዝም ብሎ ነጎደ አልተነቃነቀ፥
ሁሉንም እያየ አውቆም እያወቀ።

የኢትዮጵያ ነገር መላ እንደሌለው፥
አምላኳ አወቀላት ጉዳዩ ሌላ ነው፤
ጠላቶቿ በዙ እጅግ ጨከኑባት፥
ስለዚህ ወረደ አምላክ ሊፈርድላት፥
ምድር ዝም ትበል ይታይ ሲለይለት።

ትዕግስት አይጠቅመንም ቶሎ ያልቃልና፥
ተስፋም አይረዳንም ስጋት ያንቃልና፤
ይልቁንስ እንይ የማይታየውን፥
በእውቀት እንወቅ አይለፈን ይህ ቀን።

 

ኢሜል፥ Z@myEthiopia.com

Filed in: Amharic