በአፍና እና በአፈ-ሙዝ መካከል የሚዋልለው የኦሮሞ ፖለቲካ !!!
ሙሉአለም ገብረመድህን
–
የኦሮሞን ፖለቲካ በየሳምንቱ ‘ላይድን የተረገመ ነው’ ማለት አይጠበቅብንም! በአጭሩ በከፍተኛ ህመም ላይ ይገኛል:: ለወጣቶቹ የሥራ ዕድል መፍጠር ያልቻለው አመራር ቅራኔን እያደሰ : ጥላቻን እየጋተ ወጣቱን ዛሬም ወደ ቤቱ እንዳይገባ ጎዳናው ላይ ቆሞ ምኒልክ የሚባል አንድ ሺህ ቶን የሚመዝን ታሪካዊ “ጠላት” ሲፈልግ ይውላል::
–
ሐረር- ቆቦ መስመርም ሆነ ኮዬ ፈጨ ላይ ዛሬ ያየነው ይሄንን ነው ። ጣሊያን ራሱ በዘመኑ ያን የኩራት ምንጭ የሆነን ሰንደቅ ዓላማ በቄሮ ልክ የሚጠላው አይመስለኝም ።
–
የኦዴፓ አመራር ኦሮሞ በትግሉ ‘አሰርት’ የሚያደርገውን ነገር ለይቶ ከማቅረብ ÷ በሰጥቶ መቀበል መርሆ ለመደራደር ከመሻት ይልቅ ጠቅላይነት መገለጫቸው ሆኗል!
እናም የኦሮሞ ጥያቄ ‘የእኔ የራሴ ነው የአንተን ግን እንደራደርበት’ የሚል ነው!
–
አዲስ አበባን አምጣ“
–
ብላችሁ ልትተረጉሙት ትችላላችሁ ።
በሌላ ገፅ [ እንደሚገባኝ] የኦሮሞ ፖለቲካ በአፍ እና በአፈሙዝ መካከል እየዋለለ ይገኛል ። የውስጥ ቅራኔቸው እየተንተከተከ ነው ። ጃዋር የሽብር መተማመኛ ዜግነቱን ጥሎ ‘ኦፌኮን ይቀላቀላል’ የሚል ጥርጣሬ አይሏል ። ‘ቅራኔ ውስጥ ያሉትን ለማ መገርሳን ቢያስኮበልላቸውስ’ የሚለው ስጋትም ሌላኛው ነው ። ቄሮን በየራሱ የፖለቲካ ፍላጎት ለመቀራመት መተጋገሉ ቀጥሏል ። ይህች የአደባባይ መሸላለም ቅጥፈት ብየዋለሁ ። ማስመሰልም ሆነ ቅጥፈት ለፖለቲካቸን ባይተዋር አይደሉም ። ቅራኔው አለ!
–
ምናልባት የሰኔ 15ቱን episode 2 ፍላሚንጎ አልያም መሿለኪያ ወይንም ደግሞ ኢሊሊ ሆቴል ግድም እናየው ይሆናል ። ያኔ የኦሮሞ ፖለቲካ ተጠቃሎ ወደ አፈሙዝ ዞረ እንላለን ። ለጊዜው በአፍና በአፈሙዝ መካከል እየዋለለ ይገኛል! [ወለጋ በኦሮሚያም ሆነ በፌዴሬሽኑ አባል ስር ስለመሆኑ እርግጠኛ አይደለሁም]