>
5:13 pm - Sunday April 19, 6696

የኢትዮጵያ ጠላቶች ቤተኞቹም ከውጪ ያሉትም በሙሉ  በእግዚአብሔር የቁጣው ሰይፍ ይታጨዳሉ!!! (ዘመድኩን በቀለ)

የኢትዮጵያ ጠላቶች ቤተኞቹም ከውጪ ያሉትም በሙሉ  በእግዚአብሔር የቁጣው ሰይፍ ይታጨዳሉ!!!

 

 

ዘመድኩን በቀለ
 
….የሃገሪቱን ሰንደቅ ዓለማዋንም ልክ እንደ ዐማራው ወንድማችሁ ከፍ ከፍ በማድረጋችሁ፣ በዓረብኛ የማትምሉ በባንዳም አፍ ያማታወሩ በመሆናችሁ፣ ልክእንደ ዐማራው እናንተም ጥርስ የተነከሰባችሁ፣ ኢትዮጵያን መውደድ፣ ማፍቀር ወንጀል የሆነባችሁ፣ ሰንደቅዋን መያዝ ያስከሰሳችሁ ብሔር ብሔረ ሰቦች ነገደ ኢትዮጵያውያን በሙሉ ግን አይዟችሁ።
 * ኢትዮጵያም ሰንደቅ ዓላማዋም፣ ሃይማኖቷም ያለከልካይ ይነሣሉ። ከፍከፍም ይላሉ። 
•••
“መርፌ ወግተው፣ ኪኒን አውጠው፣ በጥይትና በቀስት፣ በመርዝና በበሽታም የምስኪን ዐማሮችን ዘር ለማጥፈት ሠርተው የነበሩ አረመኔዎችን ካሉና ከነበሩ አሁን ካሉ፣ ወደፊት እንኳ አይኖሩም፥ አሁን አጥፊዎችን የሚያጠፋ፣ ከለር ሳይመርጥ ዘርማንዘራቸውን የሚያጠፋ፣ በያሉበትም እያጨደ እንደ ስንዴ ክምር የሚከምር፣ የማያዳላ፣ ጉቦ የማይበላ ዓለምአቀፍ መቅሰፍት ከፈጣሪ ዘንድ መጥቷልና ዐማሮች ሆይ ብዙም አትጨነቁ። ለእያንዳንዱ በሠራው ሥራ በሥራውም መጠን የእጁን የሚከፍል ጌታ እነሆ በሁሉም ደጃፍ ቆሟል። ለእያንዳንዱ በሥራው ልክ እንደድካሙ መጠንም ዋጋውን ይከፍል ዘንድ እግዚአብሔር አሁን በግርማ መለኮቱ ተገልጧል።
•••
ለሆዱ አድልቶ ከጠላት ጋር አብሮ የቆመ የስም ዐማራ፣ ዐማራ ዘሩን እንዳይቀጥል በዚህ ዘግናኝ ኃጢአት ውስጥ ተሳትፎ የነበረው ሆዳም ዐማራም ካለ መቅሰፍቱ እርሱንም ከነ ዘርማንዘሩ ያጸዳለታል። እንደዶሮ ፈንግል በየጥጋጥጉ ሲፈነገል ታየዋለህ። የዘራውን አያጅድም፣ የወለደውን አይስምም። ቀባሪ እንኳን አያገኝም። ገዳይም አስገዳይም ከነዘር ማንዘሩ ያለመርፌ፣ ያለጥይት፣ ያለቦንብ በእግዚአብሔር በትር እንደቅጠል በየሜዳው ሲከመር ታየዋለህ።”
•••
እናንተ ቀሪ ዐማሮች ግን ራሳችሁን መርምሩ። በየቦታው እኚኚ አትበሉ። በወደቃችሁበት ጭቃም ላይ ተወዝፋችሁ አታለቃቅሱ። ንስሐም ግቡ። የቀደመ የአባቶቻችሁን የጥበብ መንገድ ተከተሉ። ጸሎታችሁንም አጠንክራችሁ ቀጥሉ። ከበፊቱ ይበልጥ አሁን ላይ ጠንክራችሁ ጸልዩ። ዐማራን ከእግዚአብሔር በቀር በምድር ላይ ሊረዳው የሚችል ሌላ ኃይል እንደሌለውም አምናችሁ ራሳችሁን በራሳችሁ አጠንክሩ። ወዳጄ የማን ዘር ጠፍቶ የማን ይቀራል ብለህ ነው አባዬ። በቀለኛው እግዚአብሔር ይበቀልላቸዋል። ትጠረጋለህ  !!
•••
አይደለም ዐማራን የዐማራን ዘር ለማጥፋት የደከመውን ነፍሰ ገዳይ ይቅርና እግዚአብሔር እያንዳንድሽን ከጸነስሽ በኋላ፣ እግዚአብሔር ፍሬ ከሰጠሽ በኋላ፣ በየኪሊኒኩ፣ በየመንደሩ እየዞርክ፣ መርፌ ተወግተሽ፣ ብረት በማኅጸንሽ ከትተሽ፣ ጽንሱን በጥብጠሽ፣ ፈጭተሽ ሰው የሆነን ፍጡር፣  ያጨናገፍሽ፣ ያስወረደሽና በየሽንትቤቱ የከተተሽ ነፍሰገዳይ ሁሉ አሁን ትታጨጂያለሽ። ነጠላ መልበስ አያድንም። ነፍሰገዳይ አሁን ራሱ ይሞታል። ይገደላል። አንተ እና አንቺ እናንተም አሁን ሞትን ፈርታችሁ ከቤታችሁ ብትወሸቁም፣ በሳኒታይዘር ብትዘፈዘፉም፣ በሳሙና ስታታሹ፣ ስትፈተጉ ብትውሉም፣ በማስክ አፍ አፍንጫችሁን ስትጠረዙ ብትውሉም ነፍሰ ገዳዮች ሆይ ነፍሰገዳይ ናችሁና ሞቱ እንደሁ አይቀርላችሁም። ከደጃፋችሁ ላይ ቆሟል። ሃይ በሉት። ሰላም በሉት። እየጠበቃችሁ ነው። አስተናግዱት።
•••
በአንድም በሌላ መንገድ ሆን ብሎ፣ አቅዶና ተዘጋጅቶ የዐማራን ዘር ያጠፋ ካለ ልዑል እግዚአብሔር አምላካችን የአጥፊውን ዘር ከነዘር ማንዘሩ ከምድረ ገጽ ያጥፋው። ከህይወት፣ ከትውልድ መጽሐፍም ይደምስሰው። ነበሩ ያሰኛቸው። አምላኬ ሆይ ዘር አጥፊዎችን በየሜዳው ከምረህ ውቃቸው። የሚቀብራቸው አይኑር። ዘር ያጠፋ ካለ ዘሩ ይጥፋ።
•••
የዐማራን መገፋት፣ መሳደድ፣ መገደል፣ መጨቆን፣ መበርበር፣ መገደል፣ መታሰር፣ መፈናቀል፣ አይታችሁ ተመልክታችሁ። ዐማራ ሀገሩን መውደዱ፣ ሃይማኖቱን ማፍቀሩ፣ ሰንደቅ ዓላማውን ማስከበሩ ጥርስ እንዲነከስበት፣ ቂም እንዲያዝበት ምክንያት እንደሆነበትም አውቃችሁ፣ ወንድሜ ነው፣ ወገኔነነው ብላችሁ ከዐማራ ጎን የመቆማችሁ፣ የሃገሪቱን ሰንደቅ ዓለማዋንም ልክ እንደ ዐማራው ወንድማችሁ ከፍ ከፍ በማድረጋችሁ፣ በዓረብኛ የማትምሉ በባንዳም አፍ ያማታወሩ በመሆናችሁ፣ ልክእንደ ዐማራው እናንተም ጥርስ የተነከሰባችሁ፣ ኢትዮጵያን መውደድ፣ ማፍቀር ወንጀል የሆነባችሁ፣ ሰንደቅዋን መያዝ ያስከሰሳችሁ ብሔር ብሔረ ሰቦች ነገደ ኢትዮጵያውያን በሙሉ ግን አይዟችሁ። ኢትዮጵያም ሰንደቅ ዓላማዋም፣ ሃይማኖቷም ያለከልካይ ይነሣሉ። ከፍከፍም ይላሉ። የኢትዮጵያ ጠላቶች ቤተኞቹም ከቤት ውጪ ያሉትም በሙሉ ያለገላጋይ በእግዚአብሔር የቁጣው ሰይፍ ይታጨዳሉ። ዘር ያጠፋ ሁሉ ዘሩ ይጠፋ።
•••
•በላዩ ኃጢአተኛን ሹም፤ 
•ሰይጣንም በቀኙ ይቁም። 
•በተምዋገተም ጊዜ ተረትቶ ይውጣ፤ 
•ጸሎቱም ኃጢአት ትሁንበት። 
•ዘመኖቹም ጥቂት ይሁኑ፤ 
•ሹመቱንም ሌላ ይውሰድ። 
•ልጆቹም ድሀ አደግ ይሁኑ፥ 
•ሚስቱም መበለት ትሁን። 
•ልጆቹም ተናውጠው ይቅበዝበዙ ይለምኑም፥ •ከስፍራቸውም ይባረሩ።
•ባለዕዳም ያለውን ሁሉ ይበርብረው፥ 
•እንግዶችም ድካሙን ሁሉ ይበዝብዙት። 
•የሚያግዘውንም አያግኝ፤ 
•ለድሀ አደግ ልጆቹም የሚራራ አይኑር። 
•ልጆቹ ይጥፉ፤ 
•በአንድ ትውልድ ስሙ ይደምሰስ። 
•የአባቶቹ ኃጢአት በእግዚአብሔር ፊት ትታሰብ፤ 
•የእናቱም ኃጢአት አትደምሰስ። 
•በእግዚአብሔር ፊት ሁልጊዜ ይኑሩ፤ 
•መታሰቢያቸው ከምድር ይጥፋ። መዝ 109፣ 6 -15። 
• አሜን !!
•••
ሻሎም !   ሰላም !  
መጋቢት 29/2012 ዓም
ከራየን ወንዝ ማዶ።
Filed in: Amharic