>

ጦር ሰባቂው ስዬ አብርሃ አሁን ደግሞ ምን እያለን ነው? (ዳግማዊ ጉዱ ካሣ)

ጦር ሰባቂው ስዬ አብርሃ አሁን ደግሞ ምን እያለን ነው?

ዳግማዊ ጉዱ ካሣ


“እኛ ሕወሓቶች ጦርነትን መዋጋት ብቻ ሳይሆን ጦርነትን ራሱን መሥራት እንችላለን፡፡” ስዬ አብርሃ በጉልምስናው ዘመን ከተናገራቸው ዕብሪታዊ ንግግሮች አንዱ:- “ትግራይ የሚነሳው ጦርነት ተራ ጦርነት አይሆንም፡፡” 

“ኢሳይያስ አፈወርቂ ጦርነት እንደማንፈራ ደግመን እናስታውሰዋለን፡፡” ስዬ አብርሃ በስተርጅና ዘመኑ ሰሞኑን ከተናገረው

“ንጉሥ በሠራዊቱ ብዛት አይድንም ኃያልም በኃይሉ ብዛት አያመልጥም። ፈረስም ከንቱ ነው፥ አያድንም፤ በኃይሉም ብዛት አያመልጥም።” መዝሙረ ዳዊት 33፡ 16 – 17 

“War may sometimes be a necessary evil. But no matter how necessary [it is], it is always an evil, never a good. We will not learn how to live together in peace by killing each other’s children. (Jimmy Carter) (አንዳንዴ ጦርነትን ባንወደውም አስፈላጊ ሆኖ ልናገኘው እንችላለን፡፡ ነገር ግን አስፈላጊነቱ ምንም ያህል ይሁን ጦርነት ያው ጦርነት ነውና መጥፎ ነው፤ መቼም ቢሆን ጦርነት መልካም ሊሆን አይችልም፡፡ አንዳችን የአንዳችንን ልጆች እየገደልንና እርስ በርስ እየተገዳደልን አብረን በሰላም መኖር አንችልም፡፡) (ጂሚ ካርተር) 

ስዬ አብርሃ በወያኔ ታስሯል፤ ብዙ ስቃይ እንደደረሰበትም በጊዜው ተነግሯል፡፡ ነገር ግን የእሱ እሥራትና የሌሎቻችን እሥራት አንድ አልነበረም፡፡ የነሱ እሥራትና እንግልት የታይታና የዘመድ ጥል ዓይነት ነው – የዘረኞች ዋና መገለጫ ደግሞ ይሄው ነው፡፡ እናቱ ወንዝ የወረደችበትም እናቱ የሞተችበትም ሕጻን ልቅሷቸው በመሠረቱ እኩል ነው፡፡ በእውነት ሚዛን ላይ ተቀምጠው ሲመዘኑ ግን እስረኛ ሐጎስ ፍትዊና እስረኛ አገሩ አበረ ላይ በወያኔ ይፈጸም ከነበረው መድሎ የማይናነስ ልዩነት አላቸው፡፡ እርግጠኛ ነኝ – በስዬ ጭንቅላት ትይዩ ከላይ ሆና ወደስዬ አናት የምትጸዳዳ ወያኔ አትኖርም፡፡ በጣም እርግጠኛ ነኝ – ከመለስ ወይ ከበረከት የተላከ ሦዶማዊ የስዬን ሱሪ አላስፈታም፡፡…

ወገኖቼ! ሰዎች ነንና ክፉ ሥራ መሥራት ሰውኛ ባሕርያችን ነው፡፡ ምንም ያህል በጎ ሰዎች ለመሆን ብንጥርም አንዳንዴ ልንሳሳትና ክፉ ሥራ ልንሠራ እንችላለን፡፡ ግን ግን ስንሳሳት በቅጡ እንሳሳት፡፡ ስናጠፋ ወይም ክፋትን ስንሠራ ለከት ይኑረን፤ ነገንና ትውልድንም እናስብ፡፡ ለዕርቅ የሚያስቸግር የክፋት ሥራ ከመሥራት እንቆጠብ፡፡ ቢቻልማ ደግ ለመሆን ብንሞክር በማን ዕድላችን!

ወያኔዎች በተለይ ከአማራ ጋር እንዴት መኖር እንደሚችሉ ሳስበው ይጨንቀኛል፡፡ ትንሽ ሰው ድል ሲያገኝ ምን ያህል የክፋት አቅማዳ ሊሆን እንደሚችል በተገነዘብንባቸው ባለፉት 30 ዓመታት ወያኔዎች አሸነፍናቸው ባሏቸው አማሮች ላይ የፈጸሙት የግፍ ተግባር በየትኛውም የዓለም ክፍል ማንም በማንም ላይ እንዳልፈጸመው ስድስተኛው የስሜት ሕዋሴ በሚገባ ይነግረኛል፡፡ አይሁዶች በጋዝ ጭስ አልቀዋል – እውነት ነው፡፡ አይሁዶች ሞራቸው ሣሙና ተሠርቶበታል – አንብበናልና ይህም እውነት መሆን አለበት፡፡ አርመኖች፣ አፍጋኖች፣ ኢራቆች፣ የመኖች፣ ሦርያውያን፣ ሊቢያውያን፣ ኮሶቮዎች፣ ዩጎዝላቮች፣ኩርዶች፣ቲቤታውያን፣ የደ. አፍሪካው አፓርይድ፣ ምን አለፋችሁ በሁሉም የዓለማችን ሥፍራዎች ሰው በሰው ላይ በፈጸመው ግፍና በደል እጅግ በርካታ ስቃይና እንግልት ቢመዘገብም ወያኔዎች በአማራ ላይ እንደፈጸሙት ያለ ግን በየትም አልተፈጸመም፡፡ ለዚህም ነው ትግራይ የምትከፍለው ዕዳ አንዳንዶቻችን እየታየን በደረቅ አበሳ እርጥብ መቃጠሉ ከአሁኑ እያስጨነቀን የምንገኘው፡፡ ምን አለ እንቶኔ በል – ትግራይ ብዙ ዕዳ አለባት!

ይህ በእንዲህ እንዳለ ነው እንግዲህ ስዬ ሰሞኑን ተናገረ የተባውን የተናገረውና የሰማነው፡፡

በየትኛው የትምህርት ደረጃ መጽሐፍ እንደሆነ አላስታውስም፡፡ ሦስት ልጆች የነበሩት አንድ ጅብ ነበረ፡፡ ብቻውን እየበላ ልጆቹን በርሀብ ይጠብሳቸው ነበር፡፡ በመጨረሻ ችግር ሲደርስበት ልጆቹን ይጠራና አድኑኝ ይላቸዋል፡፡ እነሱ ምናቸው ሞኝ! ብቻህን እንደበላህ ብቻህን ቻለው አሉና ጆዶ ዳባ አሉት፡፡

ቢሊዮኔሩ ስብሃት ነጋ አሁን አሮጌ ጅብ ነው፡፡ ቢሊዮነሮቹ ሌሎች ጎምቱ ወያኔዎች አሁን አሮጌ ዓሣሞች ናቸው፡፡ ሦዶማውያኑ ወያኔዎች አሁን የተያያዙት አሥረሽ ምቺው ነው፡፡ ሃያ አራት ሰዓቱ አልበቃቸው ብሎ ከወደፊት ጊዜ ሳይበደሩ አይቀሩም፡፡ መብላት፣ መጠጣት፣ መደሰት፣ መተኛት … ሁሉንም የ “መ” ህጎች ተግባራዊ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ ይህን ሁሉ የሚያደርጉትም ለ30 እና 40 ዓመታት ኢትዮጵያን በግላጭ ዘርፈው ትግራይ ውስጥ ባከማቹት ሀብት ንብረትና ገንዘብ ነው፡፡ እኚህ ዐይን አውጣዎች ከኛው በተዘረፈ መሣሪያ፣ ከኛው በተዘረፈ ገንዘብ ነው እንግዲህ ዞረው አሁንም ሊያስፈራሩን የሚሞክሩት – በገዛ ዱላችን ሊቀጠቅጡን መሆኑ ነው፡፡ ተራው ትግሬ ግን በርሀብና በድህነት እየተንገላታ መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡ ትግራይ ውስጥ እዚህና እዚያ የተተከሉ አንዳንድ ፋብሪካዎች ቢኖሩም፣ እነዚሁ ፋብሪካዎች ለተወሰኑ በዝምድናና በዓላማ ለተሳሰሩ ተጋሩ በተወሰነ ደረጃ የሥራ ዕድል ቢፈጥሩም አብዛኛውን ሕዝብ የሚያሣትፍ ዕድገትና ብልጽግና አለ ማለት አንችልም፡፡ አዲስ አበባ ላይ ከስንሻውና ከምንውየለት ጎን ተሰልፈው በልመና የተሠማሩ ትግሬዎችን ስንመለከት ወያኔዎች ለትግራይ ካመጡላት አንዱ “በረከት” ልመናና ተመጽዋችነትን እንደሆነ እንረዳለን፡፡ ሀገርን ማልማት የራስን ኪስ በዝርፊያና ስርቆት የማደለብን ያህል ቀላል አይደለም፡፡ ትግራይ የተረፋት ስሙና መከራው ነው፡፡ የሚመጣባት መከራ ደግሞ ከመቼውም የበለጠና የከፋ ነው፡፡

ስዬና ጓደኞቹ እየዛቱ ነው፡፡ በማን ላይ እየዛቱ እንደሆነ ከግምት ባለፈ በበኩሌ አላውቅም፡፡ የፈረደበት አማራ እንደሆነ ዕድሜ ለአቢይ አህመድ አመራሩ ተሽመድምዶ በሙስናና በወንዝ ልጅነት የዘመድ አዝማድ አሠራርም ተጨመላልቆ የኦነግ/ኦህዲድ የጭነት ፈረስ ሆኗል – ዱሮም ሆነ አሁን ብአዴን አማራን እንደማይወክል ግልጽ ነው፡፡ ታዲያ እነስዬ የሚፎክሩት ስለየትኛው ጦርነት ይሆን?  ጦርነቱ ቢመጣስ ከአሁን በኋላ እነስዬ ናቸው አመራር ሰጥተው የሚዋጉት? ዊስኪ በቅምጫና (በኮዳ)፣ ቁርጥ በአገልግል ይዘው ሊሄዱ ነው ወደ ጦር ግምባር? ጌታቸው ረዳ ስንተኛውን ብርጌድ ይመራ ይሆን? ጄኔራል ፃድቃን በየትኛው ጎኑ ተገላብጦ ነው ዲሽቃ የሚተኩሰውና መትረየስ የሚያስተኩሰው? እውነትም አፍ አይሞትም፡፡ ሰው በመጨረሻ የሚያጣው ተስፋን ነበር – አሁን ግን ብሂል ተለውጦና በወያኔዎች ተሻሽሎ አፍ ሆነ፡፡ ጦርነት በአፍ እንደሚያወሩት ቀላል መስሏቸዋል፡፡ መቼም ለአፍ ዳገት የለውም፡፡  

የባል ውሽማ የሚባል ነገር አለ፡፡ ምን ማለት መሰለህ – ባልና ሚስት አልስማማ ይሉና ይለያያሉ፡፡ ከዚያ ሁለቱም ወይንም ከሁለት አንድኛቸው አላስችል ይላቸውና ፍቅሩ እያገረሸባቸው በኅቡዕ እየተገናኙ ይሰራረቃሉ፡፡ ያ ዓይነቱ ግንኙነት ነው የባል ውሽማ የሚባለው፡፡ ሰዶ ማሳደድ ዓይነት ግንኙነት፡፡

ወያኔን ከአራት ኪሎ ቤተ መንግሥት አውጥቶ መቀሌ ላይ የሸጎጣት ማን ነው? ከዚያ ሁሉ ክብረትና አዛዥ ናዛዥነት ድንገት ሳይታሰብ መንጥቆ በማውጣት ወደቀደመው ደደቢታዊ ጉድጓድ ማን ወተፋቸው? ቲም ለማ ምናምን እንዳትሉ – ብአዴን ኦህዴድም አትበሉ – አቢይ ደመቀ ምንትሴም እንዳትሉ፡፡ እነሱ ራሳቸው ከየት እንደመጡና ምንስ እያደረጉ እንደሆነ ለነሱ ለራሳቸውም አሁን ድረስ ትያትር እንደሆነባቸው ናቸው፤ የገባቸው ነገርም የለም፡፡ ያ ሁሉ አፍዝ አደንግዛዊ ሥራ ከሰማይ እንጂ ከምድር አልነበረም፡፡ እርግጥ ነው በደመ ነፍስ አጋጣሚዎችን እየተከተሉ ብቻ ልክ እንደወጣት ዝንጀሮ እርምጃቸው ከወያኔ ጋር መስተካከሉን ሲረዱ ከላይ በታዘዘው ክፍተት ገቡ እንጂ ያንን ናቡከደነፆራዊ ምትሃት መሰል አገዛዝ፣ ያን ፈርዖናዊ የሰው ሥጋ በል ስብስብ፣ ያን ነፍሰ በላ የአጋንንት ጥርቅም ከአራት ኪሎ ለማውጣት አንድም አቅም አልነበራቸውም፤ የላቸውምም፡፡ ቀን ሲጥል ጉንዳንም ሱሪ ታስወልቃለችና ወያኔ ምክንያት ሆና ደርግን ያህል አፍሪካን ያንቀጠቀጠ ኃይል ደብዛው ጠፋ፡፡ ወያኔም በተራዋ አንድም ጥይት ሳይተኮስባት በንፋስ ብቻ ተጠራርጋ መቀሌ ላይ ከተመች – ገና ምኑን አየችና!

ግን ግን ታዲያ የአሁኑ ጦርነት ከማን ጋር ሊሆን ነው? ያ የሚፈራ ኃይል ከየት ነው የሚመጣው? እነስዬን ከያሉበት እያሰባሰበ እንዲህ በጦር አውርድ አዶ ከርቤ እያስጓራቸው ያለው አርማጌዲዖን ከማን ጋር የሚደረግ ይሆን? “ለልጅ ይታየዋል” አይባል ነገር! የታያቸው ነገርማ አለ፡፡

“እውነት እውነት እላችኋለሁ” ይል ነበር ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ፡፡ ከጌታየ ልዋስና እኔም እውነት እውነት እላችኋለሁ ጦርነቱ እርግጥ ነው አይቀርም፡፡ በርከት ያሉ ምናልባታዊ ግምቶችን መናገር ይቻላል፡፡ የመጨረሻው ጦርነት የሚካሄደው ግን ኢትዮጵያን ወደቀደመው ክብሯ ከሚመልሰው ልዩና መለኮታዊ ኃይልን ከተጎናጸፈ ኃይል ጋር ነው፡፡ እርሱም አንዳድ አባቶች እንደሚሉት በቀጣዮቹ ጥቂት ዓመታት ውስጥ እውን ይሆናል፡፡ ምድረ ቦርጫምና ምድር አጋንንት የትግራይ ወያኔዎች ግን በቀረቻችሁ ጥቂት ወራት ፍስሃ በፍስሀ ሆናችሁ ብሉ ጠጡ፤ ይመቻችሁ፡፡ ምሥኪኑን የትግራይ ወጣት ግን ለቀቅ አድርጉት፡፡ ለነገሩ የሚሰማችሁም የለም፡፡ ጠላ ቤት ተገኝቶ ስለኛ አወራ ብላችሁ በኮሮና ስም የምትገድሉ ጨካኞች ከእንግዲህ ፀሐይ ትወጣልናለች ብላችሁ የምታስቡ ከሆነ በርግጥም የኢትዮጵያ አምላክ በሶ ጨብጧል እናንተም ዲያሌክቲክስን በሚቃረነው ሞኝነታችሁ ጸንታችኋል ማለት ነው፡፡ እርሱን አታስቡት፡፡ ይልቁንስ በቅጡ ለመሞት ራሳችሁን ለውጡ፡፡ ተጸጸቱ፡፡ የሠራችሁትን ግፍ እያሰባችሁ በማልቀስ ንስሃ ግቡ፡፡ እንደዶንኪሾት መሆን ካማራችሁም በርቱ፡፡ የሚነሳው ጦርነት ወንድን ልጅ በወንድ ልጅ እያስደፈራችሁ፣ ሰዎች ፈቅደው ባልተወለዱበት ዘር ምክንያት ዐይንን እያፈሰሳችሁና እግርና እጅን እየቆራረጣችሁ ዜጎችን በቁም ያሰቃያችሁበት ሰይጣናዊነታችሁ የሚልክባቸው የእሳት ዝናብ ስለሆነ እንኳን በፉከራና በፉገራ እንደገና ብትፈጠሩም አታሸንፉትም፡፡ አንድን ጦርነት ለማሸነፍ ወይም በተቃራኒው ሽንፈትን ለመከናነብ የሚያስቸሉ በርካታ ተጠየቃዊ ምክንያቶች አሉ፡፡ የሰው ብዛትና የመሣሪያ ጥራት ታሳቢ ቢሆኑም ከነዚህ የበለጠም አለ፡፡ ዳዊት ጎልያድን ለምን አሸነፈ? አንዱ ሦምሶን በብዙ ጠላቶቹ ላይ ለምን ድልን ተቀዳጀ? ወያኔ ኢትዮጵያን ለምን አሸነፈ? አጥኑ፤ መርምሩ፡፡ ቋት ሞልቶ የሚፈስ ግፈኝነታችሁ ከሚያመጣባችሁ ታሪካዊ ቅጣት የምትድኑበት አንዳችም ቀዳዳ አይታየኝም፡፡ አብዝታችሁት ነበርና፡፡ “አንቺም ጨካኝ ነበርሽ ጨካኝ አዘዘብሽ፤ እንደገና ዳቦ እሳት ነደደብሽ” የሚባለው ብሂል ዕድሜው ከመቶ ዓመት ያልፋል፡፡

ያ ዕብድ ምሁር ተብያችሁ – ገብረ ችዳን ነው ስሙ ልበል – እንዲህ ብሏችሁ ይሆናል – ከፐርሽያዊ የቀድሞ ንጉሥ ኮርጆ መሆን አለበት ታዲያ፡፡ “ጦንክሩና ሎኖዚህ ኣህያ ኣማሮች ተዋጉኣቸው፤ አሁንም ከምቀደም ታሾንፋላችሁ፡፡ አንድ ትልቅ ብሔር በእግራችሁ ሥር ታስወድቃላቹሁ፡፡” – ፈገግ እያልን ታዲያ፡፡ ያ የታሪክ ምሁር በኢትዮጵያ ላይ በተለይም በነዚህ በፈረደባቸው አማሮች ላይ ያለው ጥላቻ እኮ ከእጆቹ መወራጨትና ከፊቱ መኮሰታተር ሳይቀር ነው ቁልጭ ብሎ የሚነበበው፡፡ ቀደም ባለ ዘመን አማራን እያሳዩ ይህን ገብረ ኪዳን ሳይገርፉት አይቀርም፡፡ ደግሞ “የትግራይ አባት” የሚል የቁልምጫ ስምም ተሰጥቶታል አሉ፡፡

የፐርሽያው ንጉሥ ምን አደረገ አሉ – ነቢያቱን ሰበሰበና ከአንድ ጎረቤት ሀገር ጋር ጦርነት ሊገጥም ማሰቡን በመግለጽ ድል ይቀናው እንደሆነ የወደፊቱን አይተው እንዲነግሩት ጠየቃቸው፡፡ አንድ ነቢይም “ንጉሥ ሆይ አንድ ኃያል መንግሥት ገንድሰህ ትጥላለህ” ይለዋል፡፡ በዚህ የነቢዩ ቃል የተማመነውና የተደሰተው ንጉሥ የጎረቤቱን ሀገር ገጠመ፡፡ ግን በቅጽበት ተሸነፈና ድል ከርሱ ተቃራኒ ሆነች፡፡ ከዚያም ያን ነቢይ አስጠራና “ምን ነው ጉድ ሠራኸኝ? አንድ ታላቅ መንግሥት ትጥላለህ አላልከኝምን?” ብሎ ይጠይቀዋል፡፡ ሰውዬውም ቀላል አልነበረምና “ንጉሥ ሆይ ታዲያ እኔ ምን አጠፋሁ? ይሄውና አንድ ታላቅ መንግሥት – የራስዎን መንግሥት – አላጠፉምን?” ብሎ መለሰላቸው አሉ፡፡ የወያኔው ምሁር አማራ ጠሉ አይተ ገ/ኪዳንም ይቺን ምክር ለወያኔ ሹክ ሳይልቻው አይቀርምና ይበርቱ፡፡ ወያኔን መሰሉ ዶን ኪሾት ጭራቆች መስለውት ከንፋስ ወፍጮ ጋር ጦርነት የገጠመበትን ቀጣዩን ጥቅስ ልጋብዝና ልሰናበት፤ ሰላም፡፡

 “Fortune is guiding our affairs better than we could have ever hoped. Look over there, Sancho Panza, my friend, where there are thirty or more monstrous giants with whom I plan to do battle and take all their lives, and with their spoils we’ll start to get rich. This is righteous warfare, and it’s a great service to God to rid the earth of such a wicked seed.”

“What giants?” said Sancho Panza.

“Those that you see over there,” responded his master, “with the long arms—some of them almost two leagues long.”

“Look, your grace,” responded Sancho, “what you see over there aren’t giants—they’re windmills; and what seems to be arms are the sails that rotate the millstone when they’re turned by the wind.”

“It seems to me,” responded don Quixote, “that you aren’t well-versed in adventures—they are giants; and if you’re afraid, get away from here and start praying while I go into fierce and unequal battle with them.”

Filed in: Amharic