>
5:13 pm - Thursday April 19, 8407

ነገርን ከስሩ፤ ውኃን ከጥሩ . . . [ክፍል ፩] አቻምየለህ ታምሩ

ነገርን ከስሩ፤ ውኃን ከጥሩ . . . [ክፍል ፩]

አቻምየለህ ታምሩ

የጥንቶቹ አባቶቻቸን   “ነገርን ከስሩ፤ ውኃን ከጥሩ” እንደሚሉት፤  የነገርን ስር ዘለቅ ብሎ ወደ ውስጥ  አጥልቆ በማሰብ  የበሽታውን ምንነትና እንዴትነት ደፈር ብለን በመመርመር መድኀኒቱን ለመውሰድ  ካልተዘጋጀን፤  ፍጅቱና የዘር ማጥፋቱ ስለሚቀጥል በየአደባባዩና በየመድረኩ የምናሰማውን ዋይታ አቁመን  በወጉ እንኳን እንዲያርፉ ለማይደረጉ ወገኖቻችን  ቀብር ብቻ  መዘጋጀት  ይኖርብናል። በመሆኑም በዚህ ጽሑፍ  የታሪካዊ ችግራችንን  ነጭ  ነጩን ጥቁር ጥቁሩን  በገባኝ መጠን  ለማቅረብ እሞክራለሁ።
በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በጋሞው መነኩሴ በአባ ባሕርይ የተጻፈውን «ዜናሁ ለጋላ» ያነበበ ሁሉ ዛሬ በኢትዮጵያ ምድር ኦሮሞ ባልሆኑ ነገዶች ላይ እየተካሄደ ያለውን የዘር ማጥፋት ሲታዘብ መጽሐፉ በትዝታ አራት መቶ ዓመትን ወደ ኋላ መልሶ ታሪኩ የተነገረበትን ዘመን የኖሩ ያህል የሚፈጥረውን ስሜት ዛሬ እየኖረው ያለው ያህል ቢሰማው አይፈረድበትም። የኦሮሞ የገዢ መደብ የሆነው ሉባ የጭካኔ ባሕል፣ የገዢ መደቡ ሉባ ለመሆን በሚያካሂደው የቡታ ጦርነት የሚፈጽመው አረመኔያዊ ጭካኔ ሁሉ ዛሬ ቄሮ ነን የሚሉ  አማራ ለማጥቃት የሰለጠኑ የጃዋር መሐመድ መንጋዎች የሚፈጽሙት የዘር ማጥፋት ጋር አንድ አይነት ነው።
ዐይናችን እያየ በወገናችን ላይ ሲፈጸም የምናዬው ጭካኔ ሁሉ ገዳ የሚባለው የኦሮሞ ገዢ መደብ ወታደራዊ ሥርዓት ተቋማዊ ያደረገው culture of violence ውጤት ነው። ፕሮፈሰር ሀብታሙ እንዳለው “The Oromo brought a distinct culture of violence that radically differed from Ethiopian standard of behavior of war.” [ምንጭ፡ Habtamu T(2018). “Gafat: The Forgotten Victims of Genocide”, A paper presented at Congreso internacional: Violencia colectiva y genocidio III: hacia una historia cultural del genocidio to be held at Universidad Pablo de Olavide de Sevilla Sevilla, Spain, June 07, 2018: Page 11].  የገዳ ሥርዓት ከሌሎች ወታደራዊ ሥርዓቶች የሚለየው በምርኮኞች ላይ ሳይቀር ritualized የሆነው culture of violenceን ተቋማዊ ማድረጉ ነው። ሌሎች ወታደራዊ ሥርዓቶች ጠላት እንኳ ቢሆን የምርኮ አያያዝ ሥርዓት አላማቸው። በገዳ ሥርዓት ግን ኦሮምኛ የማይናገር ሁሉ መጥፋት ያለበት ጠላት ነው።
በገዳ ሥርዓት በፊት የነበረው ሉባ ያልወረረውን ያልወረረ፣ ያላጠፋውን ያላጠፋ፣ ያልዘረፈውን ያልዘረፈ፣ ያላወደመውን ያላወደመ የሉባ መሪ ወይም አባገዳ መሆን አይችልም። ዛሬ ባገራችን የምናየው የኦሮሞ ያልሆነውን ማቃጠል፣ ማውደም፣ ሰላማዊ ሰውን በጭካኔ መግደል፣ ቤተ ክርስቲያን ማቃጠል፣ መዝረፍ፣ ወዘተ. . . ሁሉ የገዳ ሥርዓት ተቋማዊ ያደረገው የኦሮሞ የገዢ መደብ culture of violence ውጤት ነው።
እኔ በበኩሌ የጃዋር ለማሰብ ፈቃደኛ ያልሆነ መንጋ ኦሮሞ ባልሆነው ሕዝብ ላይ እያካሄደው ያለውን ጭካኔ ስመለከት አባ ባሕርይ በመጽሐፍ መልክ ትተውልን ያለፉትን ፊልም በዐይነ ሕሊናዬ የማየው ያህል ተሰምቶኛል። በመሆኑም ዛሬ እየተካሄደ ያለው ሁሉ የኦሮሞ የገዢ መደብ ወታደራዊ ሥርዓት የሆነው የገዳ ሥርዓት ተቋማዊ ያደረገው ritualized የሆነው culture of violence ውጤት ነው።
ባጭሩ ናዚ ኦነግ በጥንቱ የኢትዮጵያ ሰላማዊ ሕዝብ ላይ እያካሄደ ያለው የዘር ማጥፋት ዘመቻ ባለፉት አራት መቶ ዓመታት የመጣንበትን የኢትዮጵያን ታሪክ በቅጡ ባለማወቃችን የፈጸምነው ሐጢያት እያስከፈለን ያለ ከፍተኛ ዋጋ ነው። የጥንቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሰፋሪና መጤ እየተባለ በሕገ ወጥ ወራሪዎች የዘር ማጥፋት እየተካሄደበት ያለው አውሮፓውያን ላቲን አሜሪካና አፍሪካን መወረር ከጀመሩ በስንት ዘመናት በኋላ ወደ ኢትዮጵያ በገቡ ሕገ ወጥ ወራሪዎች ነው።
ኢትዮጵያዊ አይደለንም እያሉ በኢትዮጵያ ምድር የተተከሉ የጸረ ፋሽስትና የጸረ ቅኝ ግዛት ምልክቶችና የኢትዮጵያና የአፍሪካ አባቶች የሆኑ ጀግኖችን ሐውልቶች ሲያፈርሱ፤ የገዳ ሥርዓት ተቋማዊ ባደረገው የኦሮሞ የገዢ መደብ culture of violence እየተመሩ አውዳሚ፣ አረመኔያዊና ጭካኔ የተሞላበት የዘር ማጥፋት ዘመቻ ሲያካሂዱ የሚውሉ ወራሪዎችን ማባበሉ ማብቃት አለበት።
የኢትዮጵያን ነባር ነገዶች እያጠፉ፣ ከርስታቸው እያፈለሱ፣ በሕይዎት የተረፉትን ገርባ [ባርያ] እያደረጉ፣ ቅርስ እያወደሙና ስልጣኔ እየደመሰሱ ወደ ኢትዮጵያን የገቡትን ሕገ ወጥ ወራሪዎች ከነሱ በፊት አፍሪካንና ላቲን አሜሪካን የወረሩት አውሮፓውያን በወረራ የወሰዱትን ርስት ለባለበቶቹ መልሰው ተነቃቅለው ከአፍሪካ ምድር እንደወጡ ሁሉ እነሱም ወደ አገራችን መጥተው ለፈጸሙት የዘር ማጥፋት፣ ላጠፏቸው ነገዶች፣ ለደመሰሱት ቅርስና ሥልጣኔ ሁሉ ተጠያቂ ሆነው በወረራ ከመጡበት ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ከርስታችን ላይ ላገኙት ጥቅም አፈላማ ከፍለው ርስቱን ለባለቤቱ መልሰው አገራችን ወደሚሉት ሊሄዱ እንደሚገባ ትግል መጀመር አለብን። ርስታችንን ሰጥተን አንድነት ማምጣት ካልቻልን ያለን የመጨረሻ አማራጭ እንደ ዋርካ የተንሰራፉበትን የአባቶቻችን ርስት ለቀው ኦሮምያቸው ከባሌ በታች እንዲፈልጉ ማድረግ ብቻ ነው። ይህን በተፈጥሮ ሕግም በእግዚያብሔር ሕግም መሠረት አለው።
የደቡብ አፍሪካ ፓርላማ በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ወደ አገራቸው የገቡ ነጮች የወረሩትን የጥቁሮቹን መሬት ለቀው እንዲወጡ ሙሉ በሙሉ ወስኗል። ደቡብ አፍሪካ በደቾች የተያዘችበት ዘመን ኢትዮጵያም ከባሌ በታች በተነሱ በአባገዳ በሚመሩ ወራሪዎች የተወረረችበት ዘመን ነው። በተለይም የመጀመሪያዎቹ የአምስ አባገዳዎች ወረራ ማለትም የሜልባ፣ የሙደና፣ የኪሎሌ፣ የቢፎሌና የምስሌ ወረራ ደቾች ደቡብ አፍሪካን ከተወረሩበት ዘመን ጋር ይገጥማል።
የደቡብ አፍሪካ ጥቁሮች በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተወረረውን ሥርታቸውን ዛሬ ካስመለሱ ደቾች ደቡብ አፍሪካን በወረሩት ዘመን በአባገዳ እየተመራ በተካሄደው ወረራ የተወረሩት ባሊ[የዛሬው ባሌ]፣ፈጠጋር [የዛሬው አርሲ]፣ ደዋሮ[የዛሬው ሐረርጌ]፣ እናሪያ [የዛሬው ኢሉባቦር]፣ ቢዛሞን [የዛሬ ወለጋን] ወደ ነባር ባለቤቶቹ ሊመለሱ የማይችሉበት ምድራዊ ምክንያት ሊኖር አይችልም። እንዴውም የደቡብ አፍሪካ ፓርላማ ውሳኔ የተወረረብንን የአባቶቻችንን ባድማ ለማስመለስ precedence set አድርጎልናል።
የአውሮፓዎቹ ጥንታዊ አገር ስፔንም ዜጎቿ የአገራቸው ባለቤት ሆነው በሰላም የሚኖሩት Reconquista ባሉት እንቅስቃሴ ወራሪዎቻች ለብዙ መቶ ዓመታት የወሰዱባቸውን ርስታቸውን አንድ በአንድ በማስመለስ ነው። እኛም Reconquista በማድረግ የተወረረብንን ርሥታችንን ማስመለስ አለብን። ይህንን በኢትዮጵያ ቋንቋዎች ብቻ ሳይሆን በፈረንጆችም ቋንቋ በመጻፍ ታሪካችንን ዓለም እንዲያውቅ ማድረግ ይኖርብናል።
በሰልፍም ሆነ በአቤቱታ በምናደርገው ትግልና በምንሰጠው ምላሽ ሁሉ በኢትዮጵያ እምብርት ላይ የበቀለው «ኦሮምያ» የሚባለው እባጭ አባገዳዎች በየስምንት ዓመቱ ከባሌ በታች ካለው አገራቸው ተነስተው ነባሮቹን የኢትዮጵያ ነገዶች ባገራቸው ላይ እያጠፉና ገበሮ እያደረጉ፤ የተጋፈጧቸውን ከርስታቸው እያፈለሱ፣ በትእዛዝ ማንነታቸውን እየቀየሩና የገነቡትን ስልጣኔ ሁሉ እያጠፉ እንደ ዋርካ ተስፋፍተው በወረራ የያዙት የአገራችን ክፍል እንጂ ኢትዮጵያ የራሷ ያልነበረን አንድ ኢንች የሰው መሬት ወርራ እንደማታውቅ መናገር አለብን።
የመለስ ዜናዊ አማካሪ የነበረው የሲ.አይ.ኤው ፓል ሄንዝ ስለኦነግ አና በአጠቃላይ የኦሮሞ ፖለቲካ ሰለተመሰረተበት የውሸት ታሪክ እንደጻፈው ኢትዮጵያም ሆነ ከኢትዮጵያ ውጭ ያሉት ኦነጋውያን ያሻቸውን ሊቀረሹ ይችላሉ! ኦነጋውያንን ገና ጫካ ጀምሮ የሚያውቃቸው ፓል ሄንዝ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠረ በኀምሌ 30 ቀን 1992 ለመለስ ዜናዊ በጻፈለት ረጅም ደብዳቤ ስለኦነጋውያን ተረት ተረት የሚቀጥለውን ጽፎ ነበር፤
“The OLF tries to represent the Oromo as victimized by Menelik and never given justice for their sufferings. They are entitled to their own view of their history, but they cannot require other Ethiopian peoples to accept it. Much of their history is selective mythology. They forget that in historical terms, the Oromo are one of the newest [underlined in the original] peoples in Ethiopia. Europeans in North America and whites in South Africa have occupied their territories longer than the Oromo in most regions of Ethiopia.”
ትርጉም፤
“ኦነግ ኦሮሞን በምኒልክ የተጠቃና ለደረሰበትም ጥቃት ፍትህ ያላገኘ አስመስሎ ለማቅረብ ይጥራል። ስለታሪካቸው የራሳቸውን አመለካከት ሊኖረቻው መብታቸው ነው፤ ነገር ግን ሌሎች የኢትዮጵያ ሕዝቦችን እንዲቀበሉት መጠየቅ አይችሉም። አብዛኛዎቹ ታሪካቸው የተመረጠ ተረት ነው። በታሪክ በነባርነት አንጻር ኦሮሞ በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት ነገዶች ሁሉ በጣም አዲስ መጤ (ገብ) ሕዝብ መሆኑን ረስተውታል። አውሮፓውያን ወደ ሰሜን አሜሪካ እና ነጮች ወደ ደቡብ አፍሪካ የገቡበት ጊዜ ኦሮሞዎች በአብዛኛው የኢትዮጵያ አውርጃዎች ከሰፈሩበት ጊዜ ይረዝማል።”
ፖል ሄንዝ እንዳለው ኦነጋውያን ተረት ተረት እየፈጠሩ ታሪክ ነው ከ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በፊት ኦሮሞ ኢትዮጵያ ውስጥ ይኖር ነበር፣ ኦሮሞ ነባር ሕዝብ ነው እያሉ የሌለ ልብ ወለድ የሚፈጥሩበት ምክንያት ሕዝባችን የሚሉት የሰፈረበት ምድር የሌሎች ኢትዮጵያውያን አጽመ ርስት ስለሆነባቸው ነው። ታዲያ ተረት ተረታቸውን የሚቀረሹ በሰው ርስት ላይ ተሁኖ አይደለም። በወረራ ገብተው ባለርስት ያደረገቻቸውን ኢትዮጵያ ትፍረስ ሲሉን ኦሮምያ የሚባለው በወረራ የተፈጠረ ኢምፓዬር ፈርሶ ርስቱ ለባለቤቶቹ፤ የአውራጃዎቹ ስም ወደ ጥንተ መሰረቱ እንዲመለስ ትግል የማንጀምርበት ምድራዊ ምክንያት ሊኖር አይችልም።
Filed in: Amharic