![](https://www.ethioreference.com/wp-content/uploads/2020/08/FB_IMG_1598598874722-223x300.jpg)
መሪውን አስሮ እቅዱን መስረቅ – ልንቃወመው የሚገባ ነውረኛ የሌብነት ተግባር….!!!
![](https://www.ethioreference.com/wp-content/uploads/2020/08/FB_IMG_1598598874722-223x300.jpg)
ኤርሚያስ ለገሰ
የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ በህግ ከተቋቋመ እለት አንስቶ የተለያዩ የፓሊሲ ዶክመንቶች እያዘጋጀ እንደሆነ በተደጋጋሚ ሲገልጽ ነበር። ከእነዚህ ዶክመንቶች ውስጥ በአዲስ አበባ ህዝብ ሲመረጥ በአምስት አመታት ሊሰራቸው የሚፈልጋቸውን የቃል-ኪዳን (ማኒፌስቶ) ተግባራትን የሚዘረዝር ሰነድ ነበር።
በዚህ ማኒፌስቶ ላይ አስተያየት እንድሰጥበትና ማዳበሪያ ሀሳቦች እንዳቀርብ እድሉን አግኝቼ ነበር። በወቅቱ ይህንን ዶክመንት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ከተወያየን በኃላ ሁለት ስጋቶቼን ገልጬ ነበር።
፩: ጠቅላይ ሚኒስትሩ ” ግልጽ ጦርነት” በማለት ያስፈራሩትን ወደ ተግባር በመቀየር መሪዎቻችን ወደ ማሰር ይሸጋገራሉ።
![](https://www.ethioreference.com/wp-content/uploads/2020/08/FB_IMG_1598598896137-289x300.jpg)
እነሆ! ዛሬ ብራ መብረቁ የሆነ የህገ-መንግስት ቅቡልነት የዳሰሳ ጥናት ከአንድ ተቋም ሰማን። በማስከተል አዳነች አቤቤ ጠንካራ የኮሙዩኒቲ ፓሊስ እንደምታደራጅ ይፋ አደረገች። ዛሬ ደግሞ የሰላምና ደህንነት ምክር-ቤት ማቋቋሟን አዳመጥን።
እርግጥ መሪን አስሮ ሀሳቡን ሰርቆ በተበጣጠሰ መንገድ መፈፀም በኢህአዴግ (ብልጽግና) ደጃፍ አዲስ ባይሆንም ፤ ይሄን ነውረኛ የሌብነት ተግባር ማጋለጥ ያስፈልጋል።
በመሆኑም ለዛሬው ባልደራስ ከስድስት ወር በፊት ባዘጋጀው የአዲስ አበባ ማኒፌስቶ( 2013-2017) ውስጥ በምክር ቤቱ የመክፈቻ ቀን እና በተከታታይ 100 ቀናት ሊከናወኑ ከታሰቡት ቁልፍ ተግባራት ውስጥ በረቂቅ የቀረበውን ከብዙ በጥቂቱ ላካፍላችሁ። አጠቃላይ ማኒፌስቶውና ዝርዝር ተግባራቱ ረቂቁ(መነሻ) ሀሳቡ በምክር-ቤቱ ተሻሽሎ ሲፀድቅ ለህዝብ ይፋ እንደሚሆን የባልደራስ የውጭ አመራሮች አጫውተውኛል።
አዲስአበቤነት-ይለመልማል!