>
5:13 pm - Thursday April 18, 6335

ኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች በመዋቅሩ ተደራጅተው ለቤተ ክርስቲያን ዘብ እንዲቆሙ ቅዱስ ሲኖዶስ አዘዘ!  (አባይ ነህ ካሴ)

ኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች በመዋቅሩ ተደራጅተው ለቤተ ክርስቲያን ዘብ እንዲቆሙ ቅዱስ ሲኖዶስ አዘዘ!

አባይ ነህ ካሴ

* የሕግ ባለሞያዎች፥ በሀገር ውስጥ እና በውጪ አህጉረ ስብከት የቤተ ክርስቲያን ውክልና እየተሰጣቸው ግፈኞችን እንዲፋረዱ ወሰነ!
• በቅዱስ ፓትርያርኩ የሚመሩ ኹለት የብፁዓን አባቶች ኮሚቴዎች፣ በቤተ ክርስቲያንና በአገር ሰላም መንግሥትንና የፖሊቲካ ኃይሎችን በቀጥታ ያነጋግራሉ፤
• ሕዝብ እየተገደለና አገር እየጠፋ ያለው፣ በፖሊቲካው ትርምስ በመኾኑ፣ በቅራኔ የተፋጠጡ ኃይሎች ሰላም እንዲያወርዱ ይማፀናሉ፤ ለተገደሉ ኦርቶዶክሳውያን ካሳን፣ ለተፈናቀሉት መመለስን፣ በሐሰት ተከሰው በእስር ለሚንገላቱት መፈታተን፣ ለተደፈሩት ይዞታዎች መከበርን እንዲያነብር መንግሥትን ይጠይቃሉ፤
• የቅድመ አደጋ ማስጠንቀቂያ ሥርዓትን የመዘርጋቱ ሥራ፣ ቀደም ሲል በተላለፈው ውሳኔ መሠረት በአስቸኳይ እንዲጀመር፣ ምልአተ ጉባኤው ጠቅላይ ጽ/ቤቱን አሳስቧል፤
• ለድንገተኛ አደጋዎች እና ችግሮች ፈጣን ምላሽ እና ርዳታ የሚሰጥ አስተባባሪ አካል፣ በጠቅላይ ጽ/ቤቱ በማእከል እንዲቋቋም መመሪያ ሰጥቷል፤ በተለይ የውጪ አህጉረ ስብከት፣ ፋይናንሳዊ፣ ማቴሪያላዊ እና ሞያዊ ድጋፎችን እንዲያስተባብሩለት ተስማምቷል፡፡
Filed in: Amharic