>

የበሻሻው አራዳ ባ/ዳር ደርሷል...!?! (ወልቃይት ጸገዴ አምሀራ አብዮት)

የበሻሻው አራዳ ባ/ዳር ደርሷል…!?!
ወልቃይት ጸገዴ አምሀራ አብዮት

 
*…. ድርድሩ በኦህዴድ ብልፅግና በህወሃት የተስማሙበትና ያለቀለት ነገር ነው….!!!!
 
*…. በአማራ ክልልም ክፍተኛ ተቃውሞ ሊነሳና የእብይን ኦህዴድ መንግስት የሚያስወግድ እብዮት ሊቀሰቀስ ይችላል!
 
*…. የትዊተር ዘመቻ ሊጀመር ነው! 
የበሻሻው አላጋጭ የዛሬው የአማራ ክልል የስብስባ ንትርክ ጤና ነሳው መሰል ባ/ዳር ደርሷል…
የቀረችዋን መሬት ካላሰጠህ ከነዙፋንህ ትደፋለህ አለው መሰል ባይደን እሷን በአራዳ ቋንቋ ሰብስቦ ሊያዋያያቸው ጣና ደርሳል።
ነገር ግን የመጣበት ዋና አላማ ለሰላም ሲባል ለአንድነት ሲባል ለቀጣይ ኢኮኖሚያችን ሲባል የሚል የማባበያ ቃላቶችን ይዞ የአማራ ሕዝባዊ ኃይልን (የአማራን ልዩ ኃይል፣ ፋኖና ሚሊሻን)   ከወልቃይት በአስቸኳይ እንዲያስወጡ ለማግባባት እንደሆነ እየተነገረ ነው፤ ይህንንም እንደሚያደርግ ለአሜሪካው ፕሬዚዳንት ለጆ ባይደን ቃል እንደገባላቸው ታውቋል።
የአማራ ልሒቃን ( ብልፅግና) ይህን ሐሳብ ይቀበሉት ይሆን በቀጣይ ቀናት የምናየው ጉዳይ ይሆናል እኛም መረጃውን በንቃት እየተከታተልን ነው
የአማራው አመራርም ያዙኝ ልቀቁኝ ሲል ከርሞ ምን እንደሚመልስ እንቅልፍ አጥተን እየተከታተልን ነው።
ከዛ ትንቢቱ የደም ጎርፍ ተከሰተ ማለት እዳይደል አንተው።
አማራ ይህን አዉቆ ወራርዉ እንደቀደመዉ በሕዝባዊ ማዕበል ከመዉረራቸዉ በፊት እራሱን ጠንከር ባለመልኩ ያደራጅ ይታጠቅ ከትንሽ እስከ ከባድ መሳርያ ካለፈዉ ትምህርት የማይወስድ ከሆነ የከፋ እልቅት ይገጥመዋል በተለይ ወልቃይት ለማስመለስ ወያኔ ያለየሌለ ሃይል አጠናክራ የአሜርካንን ፊሽካ እየተጠባበቀች ነዉ ገናን ላሊበላ ጥምቀትን በጎንደር የማዘናጊያ እቅድ ነዉና አማራ በወያኔ እቅድ ተዘናግተህ የጥምቀት ጭዳ ዶሮ ትሆናለህ
ድርድሩ በኦህዴድ ብልፅግና በህወሃት የተስማሙበትና ያለቀለት ነገር ነው::
====
 በአማራ ክልልም ክፍተኛ ተቃውሞ ሊነሳና የእብይን ኦህዴድ መንግስት የሚያስወግድ እብዮት ሊቀሰቀስ ይችላል!
====
ወገኖች የአብይ አህመድ ብልፅግና ከህወህት ጋር እየተደራደረ ነው:: ድርድሩ የተስማሙበትና ያለቀለት ነገር ነው:: በኦህዴድ ብልፅግና  ድጋፍ በህወሃት ቁጥር  1 እና በህወሃት ቅጥር 2 የትግራይ ብልፅግና መካከል ውይይት ተጀመሯል::
ያ ብቻ እይደለም ከፍተኛ የአማራ ብልፅግና እመራሮችም ለጊዜው እምቡር እምቡር ቢሉም እነርሱም ማጉረምረማቸውን እያቆሙ ነው:: በአለንጋ ሾጥ ተደርገው::
ነገር ግን ታችኛውና መካከለኛው የአማራ ብልፅግና  በቀላሉ እሺ የሚል አይመስልም:: በአማራ ክልልም ክፍተኛ ተቃውሞ ሊነሳና የእብይን ኦህዴድ መንግስት የሚያስወግድ እብዮት ሊቀሰቀስ ይችላል::
ብቻ ምን አለፋችሁ የአብይ መንግስት እየወስዳቸው ያለው የንቀት አካሄድ ትልቅ ዋጋ ሊያስክፍለው ይችላል::
የትዊተር ዘመቻ ሊጀመር ነው! ዛሬ ከምሽቱ 2:00 ጀምሮ
 “ስልጣን ልቀቁ No More ብአዴን” በሚል በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር በመላው አለም ዛሬ ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ የትዊተር ዘመቻ ሊጀመር መሆኑን አስተባባሪዎች አሳውቀዋል። ለሌሎችም አጋሩ።
Filed in: Amharic