>

አለምን ያወዛገበው የእብዶች ሰነድ....!!! (ሙክታሮቩች ኡስማኖቭ)

አለምን ያወዛገበው የእብዶች ሰነድ….!!!

ሙክታሮቩች ኡስማኖቭ

 

የኛ ህገመንግስት በጣም ያስቀኛል። እነ ክፍሌ ወዳጆ፣ ፋሲል ናሁምና እንድሪያስ ይህን በተባበሩት መንግስታት ጭምር መታገድ ያለበት የእብድ ሰነድ ማዘጋጀታቸው ያስደንቀኛል። 
 
ላስረዳ:—
በአለም ላይ 206 ገደማ ሀገሮች አሉ። በአፍሪካ 55 ሀገራት አሉ። ይህ በጣም ብዙ ነው እየተባለ ይተቻል። ሰሜን አሜሪካን ካናዳን ስፋት አስቡት፣ ሁለት ሀገር ናቸው። የኛው የደንቆሮ ስራ ህገመንግስት በአንቀፅ 39 ከሰማንያ በላይ ብሄርብሄረሰቦችን የመገንጠል መብት በመስጠት በአፍሪካ ላይ 80 ሀገር ለመጨመር የሚፈልግ ከፈሳቸው የተጣሉ የመንደር ጨቡዴዎች የነደፉት ሰነድ እንጂ ሀገር ማለት ምን ማለት ነው ብለው በሚያስቡ ሰዎች የረቀቀ አይመስልም።
ለብሄር ብሄረሰብና ህዝብ ትርጉም በወጉ ሳያስቀምጥ የመገንጠል መብት ይሰጣል። ማነው ብሄር? ማነው ብሄረሰብ? ማነው ህዝብ? ማንም አያውቅም! የፈለገህን መርጠህ መውሰድ ነው። ከወሰድክ በኋላ መገንጠል ትችላለህ!
የህገመንግስቱ መግቢያ ስለአብሮነት ይሰብካል። አንድ ነበርን እጣፈንተችን አንድ ነው እያለ የአብሮነት ጋብቻን እያበሰረ 39 ላይ ሲደርስ ልንፋታም እንችላለን ይላል። ሰው እንዴት በጋብቻው ቀን የፍቺ ውልን አብሮ ይፈርማል። ለመፋታት እያቀዱ መጋባት ግራመጋባት አይደለም እንዴ?
ሃሃሃ ኢማጂን አለ ዶክሌ ሃሃ
መብቱ ለሁሉም ተሰጠ እንበል። መቼም ቼክ ተሰጥቶህ አትመንዝር፣ ስጋ ተሰጥቶህ ቢላዋውን አታንሳ አትባልም። የተፈቀደ ነገር አይከለከልምና 80 ሀገሮች ሊፈጠሩ ነው በምስራቅ አፍሪካ 😀
በአፍሪካ ካሉት 55 ሀገሮች ላይ 80 ሲጨመሩ መቶ ሰላሳ አምስት ሀገሮች!
በተባበሩት መንግስታት መቼም መመዝገባቸው አይቀርም። ተመዝግበው አመታዊ ጉባኤ ሲደረግ አስቡት። 80 ሀገሮች ንግግር ሲያደርጉ፣ 55 አፍሪካ ሀገሮች ይጠብቃሉ። 150 ከአፍሪካ ውጭ ያሉት ተራቸው እስኪደርስ ያለውን መከራ አይጣል ነው።
የኛዎቹ በቀድሞ ኢትዮጵያ በምትባል ሀገር ውስጥ የነበሩ ሀገራት ርዕሰብሄራቸው ንግግር እንዲያደርጉ ተራ ሲደለደል ሲረባበሹ አለም በሳቅ ሊያልቅ ነው። ዳውሮ አንደኛ ይናገር ሲባል በቁጠር እኔ ስለምበልጥ ይህ ለሀራችን ንቀት ነው ይላል ኦሮሞ። አማራ ልቅደም በአልፋቤት ይሁን ይላል።
ስልጤና የም መጨረሻማ አንሆንም ሲሉ አርጎባ ከአማራ ቀጥሎ መናገር ስለሚፈልግ የአማራን ሀሳብ ሲደግፍ ቅማንትና ትግራይ ይቃወማሉ። ሀረር በታሪክ እቀድማለሁ ይላል። ኝአንጋቶምና ሸካ መናገር እንጂ ቅደም ተከተሉ አያስፈልግም ሲሉ እነ የምና ቀቤና በዕጣ ይሁን ይላሉ። ይህ ክርክር አንድ ሳምንት በመውሰዱ የተባበሩት መንግስታት የመሪዎች ጉባኤ ሳይጀመር ይቀራል። አለም ይህን ውዝግብ እንደኮሜዲ ሲኒማ ፈንድሻና ፔፒሲ ይዞ ይደክማል 😀
ኦሎምፒክ ሀገራት የስማቸውን ታፔላና ባንዲራ ይዘው ሲወጡ አዲሶቹ 80 ሀገራት የሰልፉን እርዝመት በዕጥፍ ይጨምሩታል፣ ውድድሩ ወር የነበረው ወደ ሶስት ወር ያድጋል።
ፊፋም፣ ካፍም ይቸገራል 😀
የስፖርት ፌዴሬሽኖች ውይይ ውይይ አንችልም ብለው 80ዎቹ እንደገና በኮንፌዴሬሽን ተዋህደው እርስበርስ ማጣርያ አድርገው አንድ አሸናፊ ይላኩ የሚል ምክረ ሀሳብ ይመጣል ሃሃሃ ማን ከማን ያንሳል እየተባለ ይጨቃጨቃሉ።
በቡና መገኛ ሀገርነት 20 ሀገራት በአለማቀፍ ፍርድቤት ይካሰሳሉ
በጤፍ የፓተንት መብት 10 ሀገሮች በአለማቀፍ ፍርድቤት ይካሰሳሉ
በድንበር ይገባኛል 50 ሀገራት  በአለማቀፍ ፍርድቤት ይካሰሳሉ
የአለማቀፍ ዜና ተቋማት ሰበር ዜና በየቀኑ ከነዚህ ሀገራት ይመጣል
በሀገራት መካከል የግብይትና የመዘዋወር ነፃነት አስቸጋሪ ይሆናል።
ከቴፒ አከባቢ ሸካ ሀገር ተነስተው አዲሳባ ለመምጣት የሃያ ሀገራት ቪዛ ያስፈልጋል።
ቱሪስቶች ይቸገራሉ
“This country is Gamo, Gamo is known ” እያላችሁ እንግዶቹን የያዘው መኪና ዳውሮ ገብቷል ሃሃሃ
ሌላው በሰማንያ አዲሶቹ ሀገሮች መካከል አስራምናምን ጦርነት ተነስቶ ሰላም አስከባሪ ይጠፋል።
አለም ተወዛግቦ “ቆይ ይህ ሁሉ ሀገር እንዴት መጣ?”
ሲባል የብሄረሰብ መብት ለማስከበር የመጣ ነው ይባላል። በኢትዮጵያ ህገመንግስት የእብዶች ሰነድ መሆኑ ይደረስበታል።
አለም ስጋት ያድርበታል። ናይጄሪያ 200 ብሄሮች አሉኝ፣ የኢትዮጵያ ተሞክሮ ያጠፋኛል ትላለች። አጠገባችን ያለችው ኬንያ በምን ቀን ነው የእብዶች ጎሮቤት የሆንኩት ብላ ትተክዛለች (የብዙ ሀገራት ስደተኞች በማስተናገድ ድብን ብላ ትቃጠላለች)
የአለም ህዝብ ግራ ይገበዋል።
“Wait a minute. What went wrong?” እያለ አለም ይጠይቃል
ከዚያ ሰው ልክ እንደ 13 ቁጥር 39 ቁጥርን የመጥፎ እድል ምልክት ያደርጋል
Seyoum Teshome  ን 20 ሀገራት ደናቁርት ብሎ ሰደበን በሚል ያሳድደዋል
አብይ አህመድ “መደመር” ፍልስፍና ፈርሶበት ገዳም ይገባል
ደንቆሮ ሰነድ!
Filed in: Amharic