>
5:13 pm - Saturday April 18, 7131

•…ቆሻሻ ?????  (ዘመድኩን በቀለ)

•…ቆሻሻ ????? 

ዘመድኩን በቀለ

 
”…በእናንተ ምክንያት የከተማችን ገጽታ እየቆሸሸ ነው፤ ከዚህ በኋላ አንድም ተፈናቃይ ወደ ከተማችን እንዳይገባ ጥብቅ ቁጥጥር እናደርጋለን።“
 
የብአዴን ተቃውሞ… 
 
ብአዴን፦ “ወሮ ሊድያ ዐማራም ብአዴንም አይደለችም።”
 
እኔ ዘመዴእህ ዛድያ …   ምንድነች?
 
*…. 
 
“…ከምሥራቅ ወለጋ፣ ከምዕራብ ሸዋ፣ ከኦሮሚያ የተለያዩ ክፍሎች በኦሮሞ ነፃ አውጪ የኦሮሞ ልጆች አስገዳጅነት ተፈናቅለው አዲስ አበባ የገቡትና በጃንሆይ ሜዳ ላይ የፈሰሱትን የዐማራ ነገድ አባላት ካረፉበት፣ ከፈሰሱበት ስፍራ ወደ ደብረ ብርሃን ለማባረር የከተማ አስተዳደሩ በብሔር ዐማራ እንደሆነች የሚነገርላትን ባለሥልጣን መላኩ ተሰምቷል። ተላላኪዋ  መደቧ ያው ከሆዳም ዐማራ ወገን ናው ማለት ነው። ሁሌ ምክትል የበድኑ ብአዴን አባል ናት ተብዬዋ ወደ ሥፍራው የተላከችው የዋና ሓላፊ የኦሮሞው ዶ/ር ቀንአ ያደታ የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ምክትል ኃላፊ በመሆን ለስሙ የተጎለተችዋ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ መሆኗም ተነግሯል።
“…የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ጸጥታ ቢሮው የፀጥታ ዘርፍ አስተባባሪ ወ/ሮ ሊድያ ግርማ ተፈናቃዮቹ ወዳሉበት መጠለያ በመሄድ ”…በእናንተ ምክንያት የከተማችን ገጽታ እየቆሸሸ ነው፤ ከዚህ በኋላ አንድም ተፈናቃይ ወደ ከተማችን እንዳይገባ ጥብቅ ቁጥጥር እናደርጋለን።“ በማለት ስደተኞቹን በኃይል በመጫን ወደ ደብረ ብርሃን እንዲሄዱ አስደርጋለች።
“…በሩዋንዳ የዘር ማጥፋት “በረሮ” የሚል የቅጽል ስም በመስጠት እንዳጸዱት እንደጨፈጨፉት ሁሉ ለዐማራው ቀደም ሲል ህወሓት “ነፍጠኛ፣ አሀዳዊ፣ የአፄው ሥርዓት ናፋቂ፣ ወዘተ በማለት ስታጸዳው የቆየች ቢሆንም አሁን ደግሞ የህወሓት የልጅ ልጅ ሜካፓሙ፣ ዲኮራሙ ብልጽግና ለዐማራ ነገድ አባላት አዲስ የማስወገጃ ስም ማስተዋወቁ ነው የሚሰማኝ። “ቆሻሻ”  ይሄ አዲሱ የዐማራ ስም እንደሆነ ነው የሚሰማኝ።
“…”ቆሻሻው” ከኦሮሚያ ይጸዳል። እየጸዳም ነው። “ቆሻሻው” ከአዲስ አበባም ይጸዳል። እየጸዳም ነው። “ቆሻሻው” ደብረ ብርሃን እየተከማቸም ነው። ከሶማሌ ክልል ለዲሞግራፊ ለውጥ የተፈናቀሉት ኦሮሞዎች መለስ ዜናዊ ወገኖቹን “ወርቅ” ብሎ ይጠራው እንደነበረው ኦህዴድም “ወርቄ” በማለት በአዲስ አበባ ኮንዶሚንየምና በአዲስ አበባ ዙሪያ በመንግሥት ወጪ ቤት ሠርቶ ማስፈሩ ይታወቃል።
“…ውቧን አዲስ አበባ “ቆሻሻ” የተባለውና ከኦሮሚያ እየጸዳ የሚገኘው ብሔር ለደቂቃም እንዳያርፍባት መደረጉ እየታየ ነው። “የቆሻሻው” ነገድ ባለ ሥልጣናት የመንግሥቱ አገልጋይ ናቸው። ብአዴን ትልቁም፣ ጩጬው ዐብንም ጆሮ ዳባ ልበስ ብለዋል። ባልደራስ ብቻ ነው ዜጎች ቆሻሾች አይደሉም በማለት ፖሊስን ተጋፍጦ በኃይል ወደ ደብረ ብርሃን እስኪጫኑ ድረስ የተሟገተው። ብዐዴን፣ ዐብን፣ የተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ ታዋቂ ሰዎች በሙሉ “እስክንድር ነጋን” እንደታማሚ ነው የሚቆጥሩት። ለራሳቸው ዘር እየተሟገተ የሚስቁበትን ሰዎች መጨረሻ መድኃኔዓለም ያሳየኝ ዘንድ ጸሎቴ ነው።
“… እደግመዋለሁ ፣ አዲስ አበባ ሆይ ቀጣይ ተረኛ አንቺ ነሽ። እናም ከወዲሁ ደብረ ማርቆስና ደብረ ብርሃን ላይ ሰፋፊ ድንኳን ተጥሎ እንዲጠብቅሽ ተንቀሳቀሺ። ያውም ለደብረ ማርቆስ ዓባይን፣ ለደብረ ብርሃን አሌልቱን የመሻገር፣ የማለፍ ዕድል ካገኘሽ ነው። ይመራል ግን ዋጡት።
•… የሚገርመው ነገር ይሄን ጦማር ራሱ ሼር ማድረግ የሚፈራው ዐማራ ብዛቱ። ለዐቢይ አሕመድ መንግሥት እንዘጥእንዘጥ የሚለው ዐማራ ብዛቱ፣ ገንዘብ ለብልፅግናው መንግሥት የሚያዋጣው ብዛቱ። HR ምንትስዮ እንዳይጸድቅ የሚታገለው ብዛቱ። ለማንኛውም አቢቹ ነገ ፓርላማ ቀርቦ የህዳሴ ግድብ ጳራራም፣ ጲሪሪም ይልህና ለተፈናቃዮቹ የሚሆን አስለቃሽ፣ አሳዛኝ፣ ምፅፅ ምፅ የሚያስብል፣ አንጀት የሚበላ፣ ድሮስ እሱ ብቻውን ምን ያድርግ? አስብሎ የሚያደነዝዝ አዚም ይረጭበታል። የተኛውን ዐማራ ይባስ መልሶ ያስተኛዋል። ፈጣሪ ይሁንህ !!
 
የብአዴን ተቃውሞ… 
 
ብአዴን፦ “ወሮ ሊድያ ዐማራም ብአዴንም አይደለችም።” 
 
እኔ ዘመዴ ፦ እህዕ…  እና ምንድነች? 
“…ሰላም ዘመዴ … ዛሬ ስሟን ጠቅሰህ በጻፍካት እና “በእናንተ ምክንያት የከተማችን ገጽታ እየቆሸሸ ነው፤ ከዚህ በኋላ አንድም ተፈናቃይ ወደ ከተማችን እንዳይገባ ጥብቅ ቁጥጥር እናደርጋለን።“ በማለት ከአዲስ አበባ ወደ ደብረ ብርሃን እንዲባረሩ በተደረጉት ዜጎች ላይ ፀያፍ ቃል ስለ ተናገረችው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ጸጥታ ቢሮ የፀጥታ ዘርፍ አስተባባሪ ስለ ሆነችው ወ/ሮ ሊድያ ግርማ የብሔር ማንነት በተመለከተ ጥቆማ ለመስጠት ነው።
“…ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ የእኛ የብአዴን አባል አይደለችም። ወላጅ አባቷ ኮሎኔል ግርማ ትግሬ ሲሆኑ በእናቷ በኩል ደግሞ የጉራጌ ነገድ አባል ነች። ሊዲያ ባለትዳርና የሁለት ልጆች እናት ስትሆን በኦሮሞ ኮታ ኦህዴድ ተብላ ኦህዴድን ወክላ ነው ባለሥልጣን የሆነችው። የደኢህዴን አባል ናት የሚሉም አሉ። የሆነው ሆኖ ግን ሊዲያ አሁን ባለው የዘር ፖለቲካ ኮታ ከትግሬ ወገን ናት። ለዚህ ነው ለአባቷ ወገኖች አግዛ ዐማራን ቆሻሻ ያለችው። ሊድያ የእሪበከንቱ ሠፈር ልጅ ናት። ከለውጡ ወዲህ ኦሮሞ ኦሮሞ ነው የምትጫወተው። ሲበዛ ሴሰኛም ናት። መጀመሪያ በወያኔ ጊዜ የልደታ ባሕልና ቱሪዝም ሓላፊ ነበረች። እነሡ ሲወጡ የቂርቆስ ሥራአስፈፃሚ፣ ዛሬ ደግሞ የሠላምና ፀጥታ ሓላፊ ሆናለች።
“…እንዲያውም ባለ ሥልጣን ከሆነች በኋላ ኢንጂነር ባለቤቷን እያስፈራራች የትም የምትማግጥ አለሌም ከሆነች ሰነባብታለች። ስልክ ቁጥሯም 09120779** ነው። ለነገሩ እኛም ውስጥ ብአዴን ውስጥ ማለቴ ነው የሚበዛው ሹመኛ ወላጁ ትግሬ፣ ኦሮሞና፣ ሌላ ሌላ የሆነ ነው የሚበዛው። ከላይ እስከታች በሥልጣን ላይ ያሉት ከዐማራ አባት እና እናት የሚወለዱት በጣት የሚቆጠሩ ናቸው። እነሱም ወሳኝ አይደሉም። የተዋጡ ናቸው። ሥልጣንም አይሰጣቸውም።
“…አሁን ትግሬዋ ሊዲያ “…ለህይወታችሁ ዋስትና አንሰጣችሁም” በማለት ስደተኞቹን ሰድባና አዋርዳ ወደ ደብረ ብርሃን መላኳ ይታወሳል። ስደተኞቹ ደብረ ብርሃን ከደረሱ በኋላ ደብረ ብርሃን ስደተኛ ስለበዛብኝ አልቀበልም ብሎ ተመለሱ ብሏቸዋል። አውቶብሶቹም ስደተኞቹን ይዘው ወደ አዲስ አበባ ለመመለስ መንገድ ከጀመሩ በኋላ እንደገና ከፌደራል ተደውሎ ስደተኞቹን የያዘው መኪና ጫካ ላይ ቆሟል። ቀጥሎ የሚፈጠረው አይታወቅም።
“…ዐማራ መሰደጃ እንኳን ሲያጣ ይገርማል። ሌላው ብሔር ብሔረሰብ ዳር ቁጭ ብሎ ይስቃል። የዳያስጶራ ዐማራ ደግሞ ብልጽግና አይነካብኝ፣ ዐብይን ክፉ አይንካው ብሎ በአናቱ ተተክሎ ለገዳዩ ይጸልያል። ገንዘብ ያዋጣል። ጋዜጠኞች ትንፍሽ አይሉም። እነ ዐብን ሚንስትር ሆነው ተለጉመዋል። የዚህ ነገር መጨረሻው ምን ይሆን?
ሻሎም !  ሰላም !
Filed in: Amharic