>
1:21 pm - Sunday March 26, 2023

ጋዜጠኛ ወግደረስ ጤናውን ጨምሮ  የባሕር ዳር ፋኖዎች በዋስትና ከእስር እንዲፈቱ ፍርድ ቤቱ ወሰነ ጌጥዬ ያለው

 

ጋዜጠኛ ወግደረስ ጤናውን ጨምሮ  የባሕር ዳር ፋኖዎች በዋስትና ከእስር እንዲፈቱ ፍርድ ቤቱ ወሰነ

ጌጥዬ ያለው

የባልደራስ ዘጋቢ ወግደረስ ጤናው እና የአማራ ፋኖ በባሕር ዳር አባላት ፋኖ #ይገርማል በላይ እና ፋኖ #ወልደጊዮርጊስ መኮንን  ዛሬ አርብ፤ ሃምሌ 29 ቀን 2014 ዓ.ም. በአማራ መስተዳድር ጠቅላይ ፍ/ቤት ቀርበዋል። ችሎቱ በዋስትና ከእስር እንዲፈቱ የወሰነ ሲሆን የፖሊስን አስተያየት ለመስማትና የዋስትናውን አይነት ለመበየን ለፊታችን ነሐሴ 2 ቀን 2014 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

ፖሊስ ዛሬም ተጨማሪ 14 የምርመራ ቀናት እንዲሰጠው ጠይቋል። የእስረኞች ጠበቃ በበኩላቸው ሦስት ጊዜ የምርመራ ቀናት ተፈቅዶለት ማስረጃ አለማግኘቱን ጠቅሰው የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ጠይቀዋል። በመሆኑም ችሎቱ የፖሊስን ጥያቄ ውድቅ አድርጎታል።

በተያያዘ ዜና የአማራ ፋኖ አንድነት አመቻች  አመራርና አባላት የአማራ ጠቅላይ ፍ/ቤት በ25 ሺህ ብር ዋስትና እንዲፈቱ የወሰነ ቢሆኑም የፌዴራል መርማሪ ፖሊስ ለወህኒ ቤት በሰጠው ሕገ ወጥ ትዕዛዝ ምክንያት በእስር ላይ ቀጥለዋል።

Filed in: Amharic