>

የባልደራስን ጽሕፈት ቤት በኦሮሚያ ፖሊስ ተከቧል...!!! (ዘመድኩን በቀለ)

እዚህ ጋር ደግሞ ሌላ ትኩሳት…!!

የባልደራስን ጽሕፈት ቤት በኦሮሚያ ፖሊስ ተከቧል…!!!

ዘመድኩን በቀለ

“…በሰሜን ወሎ ጦርነቱ ቀጥሏል። በአዲስ አበባ ደግሞ እስክንድር ነጋ የት እንዳለ ግራ የገባው የዐቢይ አሕመድ መንግሥት በስተመጨረሻ የባልደራስን ጽሕፈት ቤት በኦሮሚያ ፖሊስ ማስከበቡ ተነግሯል።

“…ከባልደራስ ወጥተው ሌላ ባልደራስ ለመመስረት ከኢትዮጵያ እስከ አውሮጳ የተዘረፈጡት ጉደኞች ባልደራስን አፍርሰው የፕሮፌሰር በለጠውን ዐብን የመሰለ ባልደራስ ለመመስረት ጥድፊያውን ይዘዋል። ዛሬ ስምንት ሰዓት በጽሕፈት ቤቱ ስብሰባ ጠርቶ የነበረው ባልደራስ ከጠዋት ጀምሮ በሩን ከቦ የቆመው የፖሊስ መንጋ ገሚሱን አስገብቶ፣ ገሚሱን እንዳይገባ አድርጎ የገቡት በቢሮ ታፍነው መቀመጣቸው ተሰምቷል።

• እያመመው መጣ…!!

Filed in: Amharic