>

የኦነግ/ኦህዲዶች አይኪው ቢለካ … (ዳግማዊ ጉዱ ካሣ)

የኦነግ/ኦህዲዶች አይኪው ቢለካ …

ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

እሬቻችንን እያበላን የሚገኘውን የእሬቻን በዓል ጨምሮ ከሦስት ያላነሱ ሀገራዊና ሃይማኖታዊ በዓላት የሚከበሩበትን የመስከረም ወር 2015 ዓመተ ምሕረት ልናገባድድ አሥር ቀናት ያህል ይቀሩናል፡፡ ቀደምት አበው “ጉድ ሳይሰማ መስከረም አይጠባም” የሚል ሥነ ቃል ማስቀመጣቸውን ሳስበው እውነትም ይሄ መስከረም የሚባል ወር ከጉድም ጉድ የሆነ ወር ነው እላለሁ፡፡ 

ወደ ጅምሬ ከመግባቴ በፊት ለቃላት ፍቺ ልስጥ፡፡ ሕወሓት ወይንም ወያኔ ስል የሕወሓትን የትግል ሥልትና ተከታይ ውጤት የሚያራምዱ ከሰው በታች የሆኑ ባለዝቅተኛ አእምሮ ትግሬዎችን ማለቴ ነው፡፡ ብአዴን ስል በተፈጥሯዊ የአገልግሎት አበርክቶዋ ከአህያ የማያንሱ፣ በሆዳምነታቸው ከጅብና ዓሣማ የሚስተካከሉ፣ በቆዳ ቀለማቸው ከእስስት የሚዛመዱ፣ በአስተሳሰባቸው ከዶሮና ከውሻ በእጅጉ የሚያንሱ ይሁዳዎችን ማለቴ ነው፤ አማራ ይበልጡን እየተጎዳ ያለው ከውስጡ ከወጡ ብአዴናውያን የብል()ግና ፓርቲ ጉግማንጉጎችና አማራ መሰል የወያኔና ኦነግ ሠርጎ ገብ ምንደኞች መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ኦህዲድ/ኦነግ ወይም ኦነግና አህዲድ ስል ልክ እንደሕወሓቶች ሁሉ ከሰውነት ደረጃ እጅግ የወረዱ በዘረኝነት ልምሻ የተሽመደመዱ፣ በሆድና በሥልጣን ደዌ የተመቱ ኦሮሞ ወንድምና እህቶቼን ማለቴ ነው፡፡ በዚህ መሀል የበሽተኞቹ የዘረኝነት ልክፍት ያልበገረው ሰፊው የኦሮሞና የአማራ ሕዝብ፣ ለዘመናት በወያኔ ከተዞረባቸው ትብታባዊ የፕሮፓግናዳ ዘመቻ አኳያ ብዙው ወገናችን በወያኔዎች የዘረኝነት ስብከት በመረታቱ ሳቢያ በኢትዮጵያዊነት ጸንተው የሚገኙት ጥቂቶች ቢሆኑም እነዚህ ተጋሩ በዚህ ጽሑፍ ከሚነሱና ከሚብጠለጠሉ እርጉማን የዲያቢሎስ ሽንቶች ጋር አይደመሩም፡፡ ታላቁ መሃንዲስ አቶ ጊዜ ስብራታችንንና ውልቃታችንን ጠግኖ ሁሉንም ነገር ወደነበረበት በማምጣት እስኪያስተካክለን ድረስ ያለብን አበሳ ከባድ ነውና ጥቂት መታገስ ይኖርብናል፡፡ ድፍርሱ መጥራቱ፣ ሀገርም ከሞት መነሳቷ አይቀርም፡፡

ያለንበት ጨለማ ድቅድቅ ነው፡፡ ይህ ድቅድቅ ጨለማ በውስጡ ብርሃን አርግዟል፡፡ ብርሃኑ ከሚታያቸው ወገኖች ውስጥ መሆን ዕድለኝነት ነው፡፡ እናም ሊነጋ ቀኑ ደርሷልና በያለንበት ጸንተን የቻልን በጸሎትና በምህላ ራሳችንን ለፈጣሪ አስገዝተን የሀገራችንን ትንሣኤ እንጠብቅ፡፡ ከተያዘው የኃጢኣትና የክፋት ቸበርቻቻና አሼሼ ገዳሜ ታቅበን የወርቃማውን ዘመን መባቻ በተስፋ እንጠባበቅ፡፡ 

ዜማ ያሬድን የማታውቁ ካላችሁ የእሸቱ መለሰን የዶንኪቲዩብ የድንቅ ሕጻናት ዝግጅት እንድትመለከቱ እጋብዛለሁ፡፡ በዚያ ዝግጅት ከቀረቡ ሕጻናት መካከል የ3 ዓመቷን ዜማ ያሬድን የተከታተለ ሰው ሕጻኗ የተላበሰችውን የተፈጥሮ ፀጋ (ማለትም ዕውቀት) ማድነቁ አይቀርም፡፡ የታዳጊዋ አይኪው እጅግ አስገራሚ ነው፡፡ ከዚህች ልጅ አንሶ መገኘት ታላቅ አእምሯዊ መካንነት ነው፡፡ ኦነግ/ኦህዲዶች ዕድሜያቸው በአርባና ሃምሣ እየተቆጠረ አይኪዋቸው ግን ከሦስት ዓመት ሕጻንም የሚያንስ መሆኑና ሀገራችን ለነዚህ “ሰዎች” መሰጠቷ ኢትዮጵያ ምን ያህል የተረገመች መሆኗን በግልጽ ያመለክታል፡፡ በኢትዮጵያ ፖለቲካ በተለይ በአሁኑ ወቅት ሥልጣን ላይ ያሉ ሰዎችን ስታዘብ አንዳቸውም እንኳን ከእነዚህ በእሸቱ መለሰ ዝግጅት ላይ ከሚቀርቡ ሕጻናት የሚበልጥ አይኪው የላቸውም፡፡ በሆድ ማሰብ፣ ስለሆድ ማሰብና ለሆድ መኖር፣ በዘረኝነት አረንቋ መዳከር፣ ሰውን ወዶና ፈቅዶ ባልተወለደበት የዘር ሐረግ እየፈረጁ ማሰቃየትና መግደል ማሰር የትልቅ አይኪው ባለቤት ያደርጋል እስካልተባለ ድረስ አሁን ሥልጣን ያሉ ወገኖች በሙሉ ማለት በሚቻል ደረጃ ከሰው በታች ናቸው፡፡ በልተው አይጠግቡ፤ ጠጥተው አይረኩ፤ ማሰርና መግደል አይሰለቻቸው፡፡ ምን ጉዶች እንደጣለብን ሳስበው የኃጢኣት ክምራችን ጎልቶ ይታየኛል፡፡ እግዚዖ እንበል፡፡ 

በአይኪው ልኬት ፈረሶችና ዝኆኖች ወደ ሰው እንደሚጠጉ  ሲወራ ሰምቻለሁ፡፡ እነዚህ የዘመናችን ባለሥልጣናት ግን ከውሻ አይኪውም ያንሳል አይኪዋቸው፡፡ ውሻ ውሻን አይበላውም፡፡ ውሾች እርስ በርሳቸው በአጥንት ሲጣሉ ቆይተው የውጭ ጠላት ሲመጣባቸው ግን አጥንቱን ትተው በጋራ ይፋለማሉ፡፡ ውሾች በውሾች ሲሸነፉ ይንጋለሉና መሸነፋውን ይገልጻሉ፤ ያኔ አሸናፊው ተሸናፊውን በምንም መንገድ አይነካውም፡፡ ውሾች ታማኝ ናቸው፤ የፍቅር ሰዎች ማለቴ የፍቅር ፍጡራን ናቸው፡፡ ሰው ግን ከነሱም አነሰ፡፡ ከመጥፎ አሸናፊዎች ላም በዋናነት ትጠቀሳለች፡፡ በሬን ለማሸነፍ በሽዎች ዓመታት አንድ ዕድል ብታገኝ ሣር መጋጧን ትታ በሬውን ገደል ለመክተት ያለ የሌለ ጉልበቷን ትጠቀማለች፡፡ ኦነግና ሕወሓቶችም በአማራ ላይ የሚያደርጉትን ስንታዘብ ልክ እንደላሟ ነው፡፡ አማራ መሸነፉን እየገለጸ እንኳን ሊምሩት አልፈቀዱም፤ ከፈሪ አሸናፊ ይጠብቃችሁ ወገኖቼ፡፡ ማሸነፍ ብርቁ ከሆነ ሰው፣ ማግኘት ብርቁ ከሆነ ዜጋ አምላክ በኪነ ጥበቡ ይታደጋችሁ፡፡ ተሸናፊው ዘወር ቢልባቸው ግን — ምን አስቸኮለኝ ለነገሩ፡፡

ኦነግ/ኦህዲዶች ከውሻና ከድመትም ከማንኛውም ዐውሬ የሚባል ጨካኝ እንስሳም ሁሉ ያንሳሉ፡፡ አቢይና ሽመልስ የሠለጠኑና የተማሩ ይመስላሉ፡፡ ነገር ግን የቆጠሩት ፊደል ሰው ሊያደርጋቸው አልቻለም፡፡ እነሱ በሱፍ ገጭ ብለው ሰው በመምሰል አዲስ አበባ ላይ እየኖሩ በሥልክ በሚያዙትና ቀለብና ዘመናዊ የጦር መሣሪያ በገፍ በሚልኩለት ሸኔያቸው ግን አማራን በያለበት ያስጨፈጭፋሉ፡፡ ሰው የመሆን ትርጉሙ እምን ላይ ነው ታዲያ? የሚያስጨርሱት ዜጋ ከነሱ ጋርም ሆነ ከማንም ወገን ጋር ጠብ ቢኖረው እሽ ይሁን ግዴለም ይባላል፡፡ ነገር ግን የሚያልቀው አማራ ከአድማስ ወዲያ ማዶ ሀገርና ሕዝብ መኖሩን እንኳን የማያውቅ ባላገርና ከትምህርት አምባ የራቀ ምስኪን ነው፡፡ እነዚህ ሽመልሶችና ቶሎሣዎች ጠባቸው ከማን ጋር ነው ብለን እናስብ? አንድ በሰው አምሳል የተፈጠረ ሰው ሕጻናትንና አሮጊቶችን ከመሬት ተነስቶ ማረድ ከምን የመጣ ጭካኔ ነው? አገሩን ከፈለጉትስ ውጡልኝ ብሎ የማርያም በር መስጠትን ምን ዘጋባቸው? እርግጥ ነው – በሌላ በኩል ሲታሰብ እነዚህ ሰዎች የሴቴኔዝም እምነት ተከታዮች ለመሆናቸው ልንጠራጠር አይገባም፡፡ ዓለምን አንቀጥቅጦ እየገዛት የሚገኘው ሴቴኒዝም ደግሞ ክፋትን እንጂ ደግነትን ለሰው አያስተምርም፡፡ ለአጋንንቱ የጨለማ ግዛት በነፍሳቸው የተፈራረሙት እነአቢይና ሽመልስ ክፋትን ከመሥራት ቢቆጠቡ በማግሥቱ ካላቸው ምድራዊ ሥልጣንና ሀብት እንደሚነጠሉ ጠንቅቀው ያውቃሉ፡፡ እንጂ የሚሠሩት ሥራ ለመንግሥተ ሰማይ እንደማያበቃቸው ይረዳሉ፡፡ እንተዋወቃለን፡፡ አያድርስ በል፡፡ 

ኦነግ/ኦህዲዶች ሕወሓት የወለዳቸው ወይም ሕወሓትን የወለደ አካል የወለዳቸው ናቸው – ከታችኛው ዓለም የተመዘዙ የሣጥናኤል ልዑካን፡፡ ስለሆነም ከሕወሓት ጋጣ የወጣ ከሕወሓት የተሻለ አስተሳሰብና አሠራር ሊኖረው አይችልም፡፡ ከእባብ ዕንቁላል ዕርግብ፣ ከዕርግብም እባብ ሊቀፈቀፍ አይችልምና፡፡

ችግሩ ሕወሓት የወለዳቸውም ይሁኑ “ስይጥን”ና አንስቶ ያሳደጋቸው ኦነጎች በጭካኔ ጌቶቻቸውንና ፈጣሪዎቻቸውን በልጠው መገኘታቸው ነው፡፡ የመጥረቢያ ልጅ መዘለፊያ ነው – አባቱ ዳኛ ልጁ ቀማኛ ዓይነት፡፡ በደም የቆረበ ምሱ ደም ነውና ከአቢይና ሽመልስ ፅድቅን መጠበቅ የዋህነት ብቻ ሳይሆን ጅልነትም ነው፡፡ አቢይ አህመድ በተፈጥሮው እስከዚህ ጨካኝ አይደለም – የማይሆን ጎራ ተቀላቅሎ ስለተፈራረመ ግን ነፍሱን ሸጦ ለሥጋው አደረ፡፡ ስለሆነም ከሰይጣን ትዕዛዝ ሊወጣ አይችልም – በፍጹም፡፡

“አባዬ ውሸት አስተምረኝ” አለው አሉ አንድ ታዳጊ ልጅ – ወላጅ አባቱን፡፡ ትምህርቱ ወዲያውኑ ተጀመረ፡፡ “እዚያ ሰማይ ላይ አየሃቸው?” ሲል የውሸት “ዋንኦዋኑ”ን ቀጠለ አባት፡፡ “ምኖቹን?” ሲል ልጅ ጠየቀ፡፡ “ገበሬዎች በነጫጭ በሬዎች ጤፍ እያበራዩ/እየወቁ አይታይህም?” አለ አባት፡፡ ልጅ በድንጋጤ ክው ብሎ “ውይ! አባዬ፤ ዐይኔን!” አለ፡፡ አባትም ደንግጦ “ምን ሆንክ ልጄ?” ሲል ጠየቀ፡፡ “ዕብቁ ዐይኔ ውስጥ ገባ!” ሲል ልጅ መለሰ፡፡ ያኔ አባትዮው “አሃ! አንተንማ ምኑን ውሸት አስተማርኩህ፡፡ ከኔም ትበልጣለህ እኮ” በማለት መለሰለትና ትምህርቱም ብዙ ሳይገፋ በዚያው ተቋጨ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ በአራት ዓመታት ውስጥ ብቻ ወያኔ በ27 ዓመታት ከሠራው ግፍና በደል ዕጥፍ ድርብ የሚያስከነዳ የጭካኔ ተግባር በተለይ አማራው ላይ ፈጽሟል፤ አሁንም ግፍና በደሉ በስፋት ቀጥሏል፡፡ አማራ በገዛ ሀገሩ እንዳይንቀሳቀስ ከማድረግ የበለጠ ድፍረት የተሞላበት ወንጀል ሊኖር አይችልም፡፡ ይህ ድፍረት በየትም ሀገር የለም፡፡ ስደተኛ ኦሮሞ በባዕዳን ሀገሮች በአሜሪካና አውሮፓ እንደልቡ ሲንቀሳቀስ – ሲፈነጭ ላለማለት ነው – አማራ ኢትዮጵያ ውስጥ እስረኛ ነው፡፡ ይገርማል፡፡ ኅሊና ሲታወርና ሰው በጥጋብ ሲነሆልል ለካንስ እስከዚህ ያደድባል ወገኖቼ፡፡

የወያኔ ህጎች ቢያንስ መልክ ነበራቸው፡፡ የአሁኑ የኦነግ ህግና መመርያ ግን ቅጥ ያጣ ሆኗል፡፡ አያድርግብን እንጂ በቀን ስንት ጊዜ ወደሽንት ቤት መሄድ እንዳለብንና ስንት ጊዜም መተንፈስ እንዳለብን በቅርቡ መመርያና ዐዋጅ ሳያወጡ አይቀሩም፡፡ እያንዳንዱን ደምብና ህግ ስትመለከቱ አብዛኛው በሣቅ ሊገድላችሁ ይችላል፡፡ ጫት ላይ ሆነው ወይም ሀሽሽ እየማጉ ህግና ደምብ ሳያወጡ አይቀሩም መሰለኝ፡፡ ለኦሮሞ መስፋፋት ከሚያመቹ ህጎች በስተቀር ሌሎች ሁሉ እንዳይሠሩ ይደረጋሉ፡፡ መንግሥት የሚባል ነገር የለም፡፡ አንድ የኦነግ አባል ከፈለገ አንድን ነባር ህግ ሽሮ በሌላ ለራሱ በሚመቸው ተክቶት ሊያድር ይችላል፡፡ ይሉኝታና ሀፍረት የሚባል በኦነግ መንደር አይታወቅም፡፡ መግደልና ማሰር ደግሞ አቋራጭ የስኬት በሮቻቸው ናቸው፡፡ ያልታሰረ የአማራ አክቲቪስትና ጋዜጠኛ የለም፡፡ አማራም ለሽ ብሎ ተኝቷል፡፡

ለዚህ የእሬቻ በዓላቸው ሲባል አዲስ አበባን ልክ እንደግል ሣሎናቸው በመቁጠር ፍዳዋን እያሳዩዋት ነው፡፡ የአዲስ አበባ ኗሪ ግን ለመጣ ለሄደው ገዢ ሲመች ለጉድ ነው፡፡ አንድ ሊትር ቤንዚን 57 ብር ሲገባ፣ አንድ ኪሎ ሙዝ 80 ብር ሲገባ፣ አንድ ኪሎ ስኳር 120 ብር ሲገባ፣ አንድ ኪሎ ቲማቲም 70 ብር ሲገባ፣ አጭሩ የታክሲ ጉዞ 10 ብር ሲገባ፣ ያንዲት ኩሽና መሰል ቤት የወር ኪራይ 3000 ብር ሲገባ … የአዲስ አበባ ኗሪ ምን ገዶት … ፀጥ ረጭ ነው፡፡ ኦነጎች ምን እንዳስነኩን አላውቅም፡፡ አፍዝ አደንግዛቸው የተለዬ ነው፡፡ የአማራ ወደ አዲስ አበባ መግባትና የእሬቻ በዓል ምን እንደሚያገናኛቸው ደግሞ አይታወቅም፡፡ ማንም ሁን ማን አማራ ከሆንክ ሰሞኑን ወደአዲስ አበባ አትገባም፡፡ የመታወቂያ ጉዳይ አይደለም – አማራ መሆን ብቻውን ኢትዮጵያ ውስጥ ላለመኖር ዋነኛ ሰበብ እየሆነ ነው፡፡ መለስ የዐይኑ ቀለም ያላማረውን ያስርና ይገርፍ ከሀገርም ያስወጣ ነበር፡፡ እነዚህ ልጆቹ ግን በሃምሳና ስልሳ ሚሊዮን የሚቆጠር ሕዝብ እየገደሉት፣ እያሰሩትና እያሽቆጠቆጡት ይገኛሉ፡፡ የነሱም ድፍረት – የተጠቂዎቹም ጅላንፎነት ይገርመኛል፡፡ አንድ የሰባት ዓመት እረኛ አንድ ሽህና ሁለት ሽህ በጎችን በዱላ እየነረተ እንደሚጠብቅ ያህል ነው ነገሩ ሲታይ፡፡ አማራ ምን እስኪሆን እንደሚጠብቅ ማወቅ አይቻልም፡፡ እርግጥ ነው – ቀኑ ይመጣል- ደርሷልም፡፡ ያኔ እነዚህ ለጊዜው ብልጥ የሚመስሉት ጅላንፎ ኦነጎች ምን እንደሚውጣቸው አላውቅም፤ ባይገርማችሁ እሱም ያስፈራኛል፡፡ ብዙ የፈራኋቸው ነገሮች እየደረሱ አይቻለኋ! መጪው ደግሞ ይብሳል፤ ታያለህ፡፡

መልካም የእሬቻ በዓል ተመኘሁላቸው – ለኦነጎች፡፡ ግን ግን ቀን ሰጠኝ ብለህ እጅግም ግፈኛ አትሁን ወንድሜ፤ በሠፈርከው መሠፈር አለ፡፡ ጥጋብን የማይቆጣጠር ሰው ጥጋቡ ወደርሀብ ይነዳዋል፡፡ ያኔ እርሱም በተራው ያለቅሳል፡፡ በየተራ ከማልቀስ ታዲያ ልብ መግዛት ለሁሉም ይበጃልና የጠገባችሁ ሰዎች ወደኅሊናችሁ ተመለሱ፡፡ ነገ ጊዜ ላይኖራችሁ ይችላል፡፡ ሃይማኖት ባይኖራችሁ እንኳን እንደሰው ማሰብ ጀምሩ፤ ባትገነዘቡት እንጂ እናንተም እኮ ሰዎች ናችሁ፡፡ ሰው ደግሞ ከእንስሳም አንሶ መገኘት የለበትም፡፡ ለናንተው ብዬ ነው፡፡

Filed in: Amharic