>
5:13 pm - Thursday April 18, 3033

የጭራቅ አሕመድ ጭራቅነትና ያማራ ሕዝብ ዕይታ (መስፍን አረጋ)

የጭራቅ አሕመድ ጭራቅነትና ያማራ ሕዝብ ዕይታ

 

መስፍን አረጋ


ሁላችንም ጅን አለን፣ ያንተ ጅን ግን የተለየ ነው፡፡

ስብሓት ነጋ ለጭራቅ አሕመድ 

በሰይጣናዊ እሳቤው ወደር የለውም የሚባለው የወያኔው ስብሓት ነጋ ከኔ የባስክ ሰይጣን ነህ የሚለው ፍጡር የሰይጣኖች አለቃ ሊቀሰይጣን መሆን አለበት፡፡  ሕዝብ የሚወደኝ በዚህ ልክ ነው በማለት ለመታበይ ሲል ብቻ ሊደግፈው የወጣን ሰልፈኛ በጥይት የሚያስረፈርፍ ፍጡር፣ የዳቢሊስ አለቃ ሊቀዳቢሎስ መሆን አለበት፡፡  እኔን እነካለሁ ብትሉ መቶ ሺወቻችሁ ባንድ ጀንበር ትታረዳላችሁ በማለት ምንም ሳይሰቀጥጠው እንደዋዛ የሚናገር ፍጡር ደግሞ የሰውን ልጅ ማረድ ማወራረድ ስለለመደ ምንም የማይመስለው የጭራቆች አለቃ ሊቀጭራቅ መሆን አለበት፡፡

ጥድ አለቦታው ብሰና ይሆናል እንዲሉ፣ ጨዋነትና ይሉኝታ ትርጉም ያላቸው ለሚያውቃቸው ብቻ ነው፡፡  በወያኔ እና በኦነግ መዝገበ ቃላት ውስጥ ደግሞ ጨዋነትና ይሉኝታ ቴሳቸው የለም፡፡  ከአማራ ሕዝብ ዐብይ ድክመቶች ውስጥ አንዱና ዋናው ደግሞ ጨዋነት ፊረነት ለሚመስላቸው ለወያኔወች እና ኦነጋውያን አጉል ጨዋ ለመሆን አጉል መጣሩ ነው፡፡  በተለይም ደግሞ ወያናዊ እና ኦነጋዊ የሕልውና ጠላቶቹን ጥላት በመቀባት እኩይነታቸውን በግልጽ በሚያሳይ አጠራር አለመጥራቱ ነው፡፡

ጠላትህን ውደድ የሚለውን ብሂል የሚሠራው በመንግስተ ሰማያት ለሚመሰለው ለተምኔታው (utopian) ዓለም ነው፣ እዚያ ዓለም ላይ ማንም የማንም ጠላት አይደለምና፡፡  በእውናዊው (real) ዓለም ግን ጠላት ማለት ስለሚጠላህ ልትጠላው የሚገባ ማለት ነው፡፡  መሪር ጠላትህን አምርረህ ልትጠላ፣ የሕልውና ጠላትህን ደግሞ ሕልውናውን ልትጠላ ይገባልበጽኑ ያልጠላኸውን በጽኑ አትታገለውምና፡፡  

ለምሳሌ ያህል ኦነጋውያን አጤ ምኒሊክ መሪር ጠላታችን ናቸው ብለው ስለሚያምኑ፣ ተከታዮቻቸውም እንደነሱ አጤ ምኒሊክን አምርረው ንቀው አምርረው እንዲጠሉ ለማድረግ ሁልጊዜም የሚጠራቸው በስድብ፣ በማብጠልጠል፣ በንቀትና በማዋረድ ነው፡፡  በተለይም አጤ የሚለውን የከበሬታ ቅጽል ላለመጠቀም ከፍተኛ ጥረት ያደርጋሉ፡፡  በዚህ ጥረታቸው ደግሞ አመርቂ ውጤት አግኝተውበታል፡፡  ባሁኑ ጊዜ አጼ ሚኒልክን እያሳነሰና እያኮሰሰ በማዋረድ እንጅ በክብር የሚጠራ ኦሮሞ የለም ከሚባልበት ደረጃ ላይ ተደርሷል፡፡  

የኦነግ መንጋ አማራ ሲያርድ ዶሮ ያረደ የማይመስለው አለቆቹ አማራ አውሬ ነው እያሉ ደጋግመው ስላስተማሩት የማርደው አውሬ እንጅ ሰው አይደለም ብሎ በጽኑ ስለሚያምን ነው፡፡     

የኦነግ አለቃ ደግሞ የአቶ አሕመድ ዐሊ ልጅ (ወይም ደግሞ የሱ ነገር ምኑም አይታመንምና) የአቶ አሕመድ አሊ ልጅ ነኝ የሚለውን የሰው ባሕሪ የሌለው እኩይ ፍጡር ነው፡፡    ይህ የሰው ባሕሪ የሌለው እኩይ ፍጡር የአማራ ሕዝብ መሪር ጠላት ብቻ ሳይሆን የሕልውና ጠላትም ነው፡፡  ይህ የሰው ባሕሪ የሌለው እኩይ ፍጡር ቆርጦ የተነሳው የአማራን ሕዝብ እንደ ሕዝብ ከምድረ ገጽ ለማጠፋት ነው፡፡  ይህ የሰው ባሕሪ የሌለው እኩይ ፍጡር አማራን ቆረጣጥሞ እየበላ ያለ፣ አማራን ጨርሶ ካልበላ የማይጠረቃ ኦነጋዊ አውሬ ነው፡፡  ባጭሩ ለመናገር ይህ የሰው ባሕሪ የሌለው እኩይ ፍጡር በላዔ አማራ ጭራቅ ነው፡፡  

በመሆኑም የአማራ ሕዝብ ይህን ኦነጋዊ ጭራቅ በጽኑ የሚታገለው ጭራቅነቱን አውቆ በጽኑ ሲጠላው ብቻ ነው፡፡  ስለዚህም የአማራ ሕዝብ በዚህ ኦነጋዊ ጭራቅ እየተበለተ ተበልቶ እንዳያልቅ እታገላለሁ የሚል ማናቸወም ግለሰብ፣ ቡድንም ሆነ ሚዲያ ይህን ጭራቅ ሊጠራው /የሚገባው/ ጭራቅነቱን በማጉላት ብቻ ነው፡፡  በተለይም ደግሞ ይህን ኦነጋዊ ጭራቅ አንቱ፣ እሳቸው፣ እርስወ እያለ አክበሮ በመጥራት፣ የአማራን ሕዝብ ልብ መክፈል፣ መከፋፈል የለበትም፡፡  ጭራቅን የሚያከበር ጭራቅ ወይም የጭራቅ ተቀጣሪ ወይም ደግሞ ጭራቅ ወዳድ ብቻ ነው፡፡ 

ጭራቅ አሕመድ ለአማራ ሕዝብ ጭራቅ እንጅ ጠቅላይ ሚኒስትር አይደለም፡፡  ስለዚህም ይህን ጭራቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ብሎ መጥራት አድርባይነት ወይም ፈሪነት እንጅ ጨዋነት ወይም ትሕትና አይደለም፡፡  ጭራቅ አሕመድ በውሸት ለውሸት የተፈጠረ ቀጣፊና አጭበርባሪ ነው፡፡  በመሆኑም ይህን ወራዳ ፍጡር አንቱ፣ እሳቸው፣ እርሰወ እያሉ መጥራት አድርባይነት ወይም ፈሪነት እንጅ ጨዋነት ወይም ትሕትና አይደለም፡፡   

ጭራቅ አሕመድ በከረረ (chronic) አጉል አምልኮ የሚሰቃይ የከረረ የአጉል አምልኮ በሽተኛ ነው፡፡  ጭራቅ አሕመድ ሐይማኖትን ለእኩይ አላማው የሚጠቀም ሰይጣናዊ ፍጡር እንጅ ክርስቲያንም እስላምም አለመሆኑን ሰይጣናዊ ተግባሮቹ በግልጽ ይመሰክሩበታል፡፡  ይህ አፉና ምግባሩ ሐራምባና ቆቦ የሆነ ሰይጣናዊ ፍጡር፣ ዘወትር የሚያወራው ስለ መጽሐፍ ቅዱስና ቁርዓን ቢሆንም፣ የሚጓዘው ግን በክርስቶስ ወይም በነብዩ ሙሐመድ መንገድ ሳይሆን በሰይጣን መንገድ እንደሆነ ማየት ለሚፈልግ ሁሉ በገሃድ የሚታይ ግልጽ ነው፡፡  በመሆኑም ይህ ሰይጣናዊ ፍጡር ማድያቱን ለማጥፋት ባማራ ሕጻነት ደም በየቀኑ ይታጠባል፣ ተባዕታዊ ስሜቱን ለማነሳሳት (ወይም ደግሞ የሱ ነገር ምኑም አይለይምና አንስታዊ ስሜቱን ለማነሳሳት) የአማራ ሕጻናትን ሐሞት በየዕለቱ ይጠጣል፣ ሰይጣናዊ ምሱን ለመቅመስ ደግሞ የአማራ ሕጻናትን ኩላሊትና ጉበት ዘወትር ይመገባል እየተባለ የሚናፈሰው አሰቃቂ ቢሆንም፣ እውነትነቱ ግን ሚዛን ደፊ ነው፡፡   

ጭራቅ አሕመድ የአማራ ሕጻነት በታረዱ ሰሞን ከእይታ የሚጠፋው ወሸባ ገብቶ በደማቸው እየታጠበ፣ ሐሞታቸውን እየጠጣ፣ ኩላሊታቸውንና ጉበታቸውን እየበላ፣ አጥንታቸውን አቃጥሎ እየታጠነ ባይሆን እንጅ ቢሆን አያስገርምም፡፡  ከተወሸበበት ሲወጣ ደግሞ ፊቱ እንዳበባ ፈክቶ አበባ የሚተክለው ለጭራቃዊ አማላኩ ምስጋናውን ለመግለጽ፣ በዚያውም ደግሞ ልጆቹ በታረዱበት በአማራ ሕዝብ ቁስል ላይ እንጨት ለመስደድ ባይሆን እንጅ ቢሆን አያስገርምም፡፡    

ስለዚህም፣ ለአማራ ሕዝብ ሕልውና እንታገላለን የምትሉ ግለሰቦችም ሆናችሁ ቡድኖች፣ እባካችሁን ተለመኑ፡፡  የአማራ ሕዝበ መሪር ጠላት የሆነውን ጭራቅ አሕመድን ዶክተር፣ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ እሳቸው፣ እርስወ፣ አንቱ እያላችሁ በማይገባው ክብር በመጥራት፣ የአማራ ሕዝብ መሪር ጠላቱን አምርሮ እንዳይጠላውና እንዳይታገለው አታድርጉት፡፡  

ጭራቅ አሕመድ የአማራን ሕዝብ ሕልውና ጥያቄ ውስጥ ለማስገባት የቻለው የሕልውና ጠላቱ እሱና እሱ ብቻ መሆኑን የአማራ ሕዝብ በጽኑ ተረድቶ በጹኑ ስላልታገለው ብቻ ነው፡፡  የአማራ ሕዝብ የሕልውና ጠላት ወያኔም ኦነግም ሳይሆኑ ጭራቅ አሕመድ ነው፡፡  የአማራ ሕዝብ ጭራቅ አሕመድን ከጫንቃው ላይ ካወረደ፣ ወያኔና ኦነግ እዳቸው ገብስ ነው፡፡  መለስ ዜናዊ ሲሞት ወያኔ እንደፈራረሰ፣ ጭራቅ አሕመድም ሲወገድ ከመሬት አንስቶ ሰማይ ያደረሰው ኦነግና፣ ከሞት አፋፍ አንስቶ እንዲያንሰራራ ያደረገው ወያኔ ሁለቱም ፍርስርሳቸው ይወጣል፡፡  

ግራኝ አሕመድ ዛንተራ ላይ ወደቀ፡፡  ጭራቅ አሕመድስ የሚወድቀው የት ይሆን?  ሰንጋተራ?  

ኒወርከኛ (The New Yorker) የተሰኘው ያሜሪቃ መጽሔት ጭራቅ አሕመድን በተመለከተ በቅርቡ (September 28, 2022) በፈነተተው ረዘም ያለ እንቶ ፍንቶ ላይ እኔ ስልጣን ስለቅ ሚሊዮኖች እንደሚያለቅሱ መቶ በመቶ እርግጠኛ ነኝ ማለቱን ጽፏል፡፡ (“When I leave office, I am one hundred percent sure – one hundred percent sure – that millions of Ethiopians will cry”).   ውነት ተናግሮ የማያውቀው ውሸታሙ ጭራቅ አሕመድ እዚህ ላይ ግን ውነት ተናግሯል፡፡  ጭራቅ አሕመድ ሲወገድ ሚሊዮኖች እንደሚያለቅሱ መቶ በመቶ በርግጠኝነት መናገር ይቻላል፡፡ ለቅሷቸው ግን የሐዘን ለቅሶ ሳይሆን፣ ትልቁ ፀራማራ ጭራቅ ስለተወገደ የደስታ ለቅሶ ነው፡፡  

መስፍን አረጋ

mesfin.arega@gmail.com

Filed in: Amharic