>

"ከኦሮሞ ነገድ ዉጭ ያለዉን ሁሉ ጠርገን ከአዲስ አበባ እና ዙሪያዉ ማባረር አለብን...! ሽመልስ አብዲሳ  በኦህዴድ ስብሰባ ላይ (ሸንቁጥ አየለ)

“ከኦሮሞ ነገድ ዉጭ ያለዉን ሁሉ ጠርገን ከአዲስ አበባ እና ዙሪያዉ ማባረር አለብን…!

ሽመልስ አብዲሳ  በኦህዴድ ስብሰባ ላይ 

 *… የቤት ፈረሳዉ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ”

ሸንቁጥ አየለ


በአዲስ አበባ እና ዙሪያዉ የአማራ፣ጉራጌ፣ወላይታ፣የስልጤ፣ጋሞ፣ ትግሬ :አገዉ፥ ሀረሪ፥ ሶማሌ፥ አፋር እና የሌሎችንም ዜጎች መኖሪያ ቤቶች፡   በኃይል በማፍረስ በሚሊዮኖች እንዲፈናቀሉ ተደርጓል።በተለይም ከታህሳስ 2015 ጀምሮ በሽህ የሚቆጠሩ ቤቶችን በጣም በፍጥነት እየፈረሱ ነዉ፥፥ በባለ ጊዜዎቹ የኦሮሞ  አክራሪ ፖለቲከኞች፥፥

የኦሮሞ ተወላጅ የሆኑ ቤቶች አይፈርሱም፥፥ የኦሮሞ ነገድ የሆኑ ቤቶች እየተለዩ ይተዋሉ፥፥አክራሪ የኦሮሞ ፖለቲከኞች በአጋጣሚ እጃቸዉ ላይ የወደቀዉን ስልጣ ተጠቅመዉ ሌሎች ነገዶችን ከኢትዮጵያ የማጥፋት እና አፓርታይድን በኢትዮጵያ የመመስረት ፍላጎታቸዉ  እዉን ለማድረግ እንደ አበደ ዉሻ እየተክለፈለፉ ነዉ፥፥

የሌሎች ኢትዮጵያዊ ነገዶች ቤቶች ግን በሀይል ይፈርሳሉ፥፥ የዜጎች እቃ፥ ልብሳቸዉ እና ዐጠቃላይ ቤታቸዉ ከቤቱ ጋር እንዲወድም ይደመሰሳል፥፥ በብልዶዞር እና በብዙ እፍራሽ ግብረ ሀይል፥፥ከአምሳ አመታት በላይ የኖርንበት ቤት ለምን ይፈርሳል፥ ይዞታዉን የያዝነዉ ከአሴ ሀይለስላሴ ጊዜ በፊት ነዉ ብለዉ የሚጮሁ ዜጎች ደግሞ በአክራሪ የኦሮሞ ፖለቲከኞች በጅምላ በጥይት ይረሸናሉ፥፥ ይጨፈጨፋሉ፥፥

የህዝቡን ቤት ካፈረሰ ንብረቱን አብረዉ ካወደሙ ብህWላ ደግሞ ያፈረሱትን ቆርቆሮ በመዉሰድ የኦሮሞ አክራሪ ፖለቲከኞች ይከፋፈሉታል፥፥

ከአክራሪ የኦሮሞ ፖለቲከኞች መሃል አንድም ተዉ ይሄ ነገር ብሁዋላ መዘዝ ያመጣብናል የሚል እንድ እንኳን የለም፥፥ አባገዳዉ፥ ኦህዴዱ፥ ኦነጉ፥ ኦፌኮዉ፥ጀዋራዊዉ፥ መራራዊዉ፥ ብቻ ሁሉም ተባብረዉ የሌሎች ኢትዮጵያዉያን ነገዶችን በማጥፋት በአንድ ልብ ቆመዋል፥፥

እስከ 15 እና 20 ዓመት የኖሩበት ቤታቸውን ጨምሮ በሽህ የሚቆጠር ቤት እየፈረሰ በመሆኑ ህዝቡ በከፍተኛ ችግር ላይ ነው የሚሉት ነዋሪዎች በስቃይ ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

ሰሞኑን ብቻ በአዲስ አበባ ላይ የተሰራዉን ግፍ ለመጥቀስ፥

1) በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ ወረዳ 03 ጀሞ ተራራ መድሃኒያለም ከ 4500 በላይ ቤቶችን አፍርሰዋል፥፥ ብዙዎችንም ገለዋል፥፥ ንብረታቸዉን እብረዉ እዉድመዋል፥፥ ያፈረሱትን ቆርቆሮም ለአክራሪ የኦሮሞ ፖለቲከኞች አከፋፍለዋል፥፥

2/ በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ ወረዳ ፋኑኤል ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ከ 3500 በላይ መኖሪያ ቤቶች ፈርሰዋል፥፥ አሁንም እያፈረሱ ሲሆን ቤታችን ለምን ይፈርሳል የሚሉትን እየገደሉ ነዉ፥፥

3)  ሰበታ ክ/ከተማ፣ ገዳፈቻ ወረዳ ወለቴ ቀበሌ ልዩ ስሙ አጃምባ አካባቢ   ከ 3200 በላይ ቤቶች ፈርሰዋል።

4/ሰበታ ወረዳ 08 ቀበሌ፣ጎጥ 6፣እንቁ ገብርኤል አካባቢ ከ2000 በላይ ቤቶች እንዲፈርሱ ተደርጓል።

5/ ቤት በፈረሰባቸዉ በተለያዩ አካባቢዎች ቤታችን አለህግ ለምን ይፈርሳል ያሉ  ከመቶ በላይ ዜጎች በቀጥተኛ ተኩስ በግፍ ተጨፍጭፈዋል፥፥

ይሄን ሁሉ የቤት ማፍረስ የንብረት ማዉደም ስራ የሚሰሩት እየመረጡ  በአማራ፣ በወላይታ፣በጉራጌ፣ በጋሞ፣በትግሬ፥ በሲዳማ፤  በስልጤ እና በሌሎች ኢትዮጵያዊ ነገዶች ላይ ነዉ፥፥

ይሄም ሌሎች ነገዶችን የማጥፋት ስራ ግልጽ ፖሊሲያቸዉ መሆኑን ሲያስረዳ ከኦሮሞ ነገድ ዉጭ ያለዉን ሁሉ ጠርገን ከፊንፊኔ አዲስ አበባ ማባረር አለብን” ሲል በኦህዴድ ስብሰባ ላይ ሽመልስ አብዲሳ  በታላቅ ድንፋታ ተናግሯል፥፥ በተለይም ሰሞኑን ከአማራ ክልል በዉርደት የተባረረዉ ሽመልስ አብዲሳ አክራሪ የኦሮሞ ፖለቲከኞችን ሰብስቦ “የኦሮሞ የበላይነት እዉን ይሆን ዘንድ አዲስ አበባ ላይ ያሉ ሌሎች ነገዶችን ሙሉ ለሙሉ ጠርገን ማባረር አለብን፥፥ ለዚህም ቤት ፈረሳዉ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት” ሲል መናገሩ ተዘግቧል፥፥

Filed in: Amharic