>

መነበብ ያለበት የመምህር ዘመድኩን በቀለ ርዕስ አንቀጽ

“ርዕሰ አንቀጽ”

“…የሚገርም ተአምር እኮ ነው። ያን ገድለን ቀብረነዋል፣  እንዳይነሣ አድርገን ደምስሰነዋል፣ ደፍቀነዋል፣ በማንነቱ አሸማቀነዋል፣ ከሁሉ ነገር አሳንሰነዋል፣ ስሙን በዓለም አጥፍተናል፣ መድረሻ አሳጥተነዋል፣ በሁሉ ዘንድ በጥርጣሬ እንዲታይ አድርገነዋል፣ መውጫ መግቢያ አሳጥተነዋል፣ ከሥልጣን አባረነዋል፣ ከሃገር ከምድሩ አፈናቅለነዋል። ከእንግዲህ የእኛ የአናሳዎቹ ባርያ ነው፣ ገረድ ነው፣ አሽከር ነው፣ ዘበኛ ነው፣ ተላላኪ ነው፣ ከዙፋኑ ፈንግለነዋል፣ ከተሰቀለበት ፈጥፍጠነዋል፣ ከወንበሩ አሽቀንጥረነዋል፣ ከከፍታው አውርደነዋል።

“…ባህሉን ውጠናል፣ ሃይማኖቱን አራክሰናል፣ ቤተ እምነቱን አቃጥለናል፣ አውድመናል፣ የሃይማኖት አባቶቹን አርደናል፣ ገድለናል፣ አማኞቹን ክርስቲያን የሆኑትን በቤተ ክርስቲያን እስላሞቹን በመስጊድ አብረን አቃጥለናል። ሼኩን ቄሱን ልክ አግብተናል፣ ሲኖዶሱን አራት ቦታ፣ መጅሊሱን ሁለት ቦታ ከፍለንበታል፣ ጳጳሱን ከኦሮሞ፣ አባረናል፣ ሙፍቲን ከመጅሊሱ ጠልዘን በኦሮሞ ተክተናል። ህጻናት በምድሪቱ እንዳይወለዱ፣ የተወለዱትም እንዳያድጉ አድርገናል። ነፍሰጡር ሴቶቻቸውን በህይወት እያሉ ሆዳቸውን ዘንጥለን ጽንሱን ዘርግፈን ጭካኔያችንን እንዲያዩ ጽንሱን በልተናል፣ ደሙን ጠጥተናል፣ ልብና ኩላሊት ጨጓራቸውንም በልተናል።

“…አዎ ይሄን ሁሉ ያደረግንበት፣ እንዲሰደድ፣ ወደ ዘብጥያም በገፍ እንዲገባ ያደረግነው ዐማራ ከእንግዲህ አይነሣም፣ ሞቶ በስብሶ ይቀራል ብለው ነበር ህዳጣኑ ተኮፍሰው የተቀመጡት። ዐማራን አርብ ዕለት ሰቅለውት ወደ መቃብር ስላወረዱት በቃ ከእንግዲህ ወዲያ አይመጣም ብለው ደምድመው ያለቀለት መስሏቸው ነበር እግራቸውን ዘርግተው በቁልቋል በለስና ጫታቸውን ይበሉ ይቅሙ የያዙት። በተለይ በዕለተ ቅዳሚት ሰንበት የስቅለቱ ዋዜማ ማለትም ከሻሸመኔው ጭፍጨፋ፣ ከማይካድራው፣ ከጭናው፣ ከወለጋው ጭፍጨፋ በኋላ ዐማራው ፀጥ ብሎ እኔ ነኝ ሳይል፣ አርንጓዴ ቢጫ ቀይ ሰንደቅ ዓላማ አንግበው ከሚዞሩ ፌክ ኢትዮጵያኒስቶች ስር ቱስቱስ ሲል ሲያዩት፣ በሚጢጢዋ የትግሬ ነፃ አውጪ በህወሓት ሳይቀር ሲታረድ ሲገደል፣ በሚጢጢው የኦሮሞ ነፃ አውጪ ነኝ ባይ ኦነግ ሲጨፈጨፍ፣ ሲፈናቀል እኔ ነኝ የሚል የሚናገር፣ የሚተነፍስ፣ የሚሟገትለት በጠፋ ጊዜ አይተው ይኸው አላልናችሁም ዐማራ ቢኖር ይነሣ ነበር። ይፋለመን ነበር። በማለት በኩራት ደነፉ፣ ሸለሉ፣ አሽላሉም። የስቅለቱ ማግስት ቅዳሜ ነዋ ለዐማራ።

“…እነ ጉራጌ፣ እነ አፋር፣ እነ ሱማሌ፣ እነ ደቡብ ሙሉ፣ እነ ጋምቤላ፣ እነ ጉምዝ ሳይቀሩ ትግሬና ኦሮሞዎቹ ዐማራ የለም ያሉት ለካ እውነት ነው በቃ ብለው ደምድመው ነበር። ጉምዝም በቀስት፣ ሱማሌም በሰይፍ፣ ሲዳማም በቤንዚን ዐማራን በአደባባይ ገድለው፣ አርደው፣ አቃጥለው ግብረመልስ ስላላገኙ በቃ ዐማራ ሞቷል፣ በስብሷል፣ ተቀብሯል፣ ተደምስሷል ብለው ወስነው ነበር። እነ አሜሪካም በሩቅ፣ እነጣልያን፣ እንግሊዝ፣ ጀርመን ፈረንሳይም፣ ስዊድን፣ አየርላንድም ከእንግዲህ ትግሬን ነው መጠጋት፣ ኦሮሞን ነው መወዳጀት፣ እንጂ ዐማራማ ማፉሽ ኪላ፣ ኤለም ዐማራ ብለው ወስነው ነበር።

“…የዐማራ ሞት ለ CNN, BBC, ALJEZIRA, ወዘተ ዜና አይሆንም ነበር። አንድ ትግሬ በክልተ አውላሎ እንቅፋት ሲመታው እንዴት እንቅፋት ሊመታው ቻለ? አጥኚ ቡድን ይላክ፣ ሰበር ዜና ይሠራ፣ ሰማንታ ፓወር ከ USAID, አንቶኒ ብሊንከን ከአማሪካ ውጭ ጉዳይ ምኒስትር፣ አየርላንድ በጠቅላይዋ፣አንቶንዮ ጉታሬዝ የተባበሩት መንግሥታትን አስቸኳይ ስብሰባ፣ የአውሮጳ ኅብረትም እንቅፋት በመታው ጎይቶም ዙሪያ እንዳሳበው መግለጫ የሚያወጡቱ ለዐማራ ሲሆን አይናቸው ጨለማ፣ እግራቸው ቄጤማ ይሆን ነበር። ከጨረቃ በሳታላይት ያነሳነው የሆነ የአፈር ክምር በወልቃይት ምድር አይተናል። ምንአልባትም በትግሬዎች ላይ ጄኖሳይድ ተፈጽሞ ሊሆን ይችላል ብሎ በጌስ መግለጫ የሚያወጡት የዓለም ሰብአዊ መብት ተቆርቋሪ ድርጅቶች እንኳ ዐማራ በኢትዮጵያ ትኩስ የሬሳ ክምር በቪድዮ፣ በፎቶ እያዩ ሟች ዐማራ ስለሆነ ብቻ ያንን የፈረደበት “ዓድዋን እያስታወሱ በልባቸውም እሰይ ኤታባቱንስና ደግ ሞተ፣ ተጨፈጨፈ፣ እንዲህ ነበር ያኔ እኛን ያደረገን በሚል ስሜት ይረካሉ እንጂ ዐማራ ሞተ አይሉም።

“…ዐማራው ፓርቲ የለውም መብቱን የሚጠይቅለት። ብአዴን የሚባል ነበር እሱ ገረድ ነው፣ ለላንቲካ፣ ለይስሙላ ትግሬዎቹ የፈጠሩት፣ ኋላ ኦሮሞዎች ትግሬን ከባርያው፣ ከገረዱ ብአዴን ጋር አባረው ሲነግሡ መልሰው ያንኑ የህወሓት ገረድ፣ ባርያ ብአዴን የቤት ገረድ፣ የውጭ አሽከር አደረጉት። እንኳን ስለዐማራ ሊናገር ለራሱም ተጨፍጫፊ ነበር። አብን የሚባል በድኑ ብአዴን የፈጠረው ዲቃላ ልጅ ነበረው። የእንግዴ ልጅ፣ ሳይወለድ የሞተ፣ የጨነገፈ፣ እናም ዐማራ ተከራካሪም አልነበረውም። የሚገርመው ደግሞ ቢገድሉት አያልቅ፣ ቢያፈናቅሉት አይጠፋ፣ ቢያስሩት አይሞላ፣ አይጎድል፣ የጨነቀ ነበር ለአራጅ ገዳዮቹ። ዐማራ ነኝ ማለት ሰሚውን ሳይሆን ባዩን ያሸማቅቅ ያስደነግጥም ነበር።

“…እሁድ መጣልሃ ወዳጄ፣ አርብ አልፎ፣ የመከራ፣ የስቅለት፣ የድብደባው፣ የመዋረድ፣ የመናቅ፣ ምራቅ የመትፋት ዕለት አልፎ፣ የጸጥታው ዕለት ቀዳሚት ሰንበትም አልፋ እሁድ መጣልሃ ወዳጄ። የዐማራ ትንሣኤ ዕለት መጣልህ። መቃብር ክፈቱልኝ፣ መግነዝ ፍቱልኝ የለም። ብድግ በቃ ብድግ ብሎ ተነሣልሃ ዐማራ፣ እንደ መብረቅ ብልጭታ ብድግ አለልህ። የመቃብሩ ጠባቂ የትግሬ ነፃ አውጪና ኦሮሞ ነፃ አውጪ የት ይግባ? በዐማራ ላይ ድንጋይ ጭኖ፣ መከራ ጭኖ፣ በሎቤድ፣ በዶዘር ላዩ ላይ ተቀምጦ ዐማራ እንዳይነሣ ይጠብቅ የነበረው ሁላ ዐማራ ሲነሣ ወጥ በወጥ ሆነልሃ። ምድረ ኩርማን ኩርንችት ሁላ ዝሆኑን ዐማራ እንዴት ይቋቋመው?

“…አሁን ዐማራው አይነጥላው ተገፈፈለት፣ ፋኖ የተባለ የቀደመ ልጁ ተነሣለት። በደቂቃ ውስጥ ብአዴንን ስደተኛ ያደረገ፣ መላ ዐማራን የተቆጣጠረ፣ የሃገሪቱን መከላከያ ሠራዊት ከጥቅም ውጪ ያደረገ ዐማራ ተወለደ። ተነሣ ዐማራ፣ የዐማራን ትንሣኤ እንጠብቅ የነበርን እኛ የምሥራቅ ሰዎችም እጅግ ደስ አለን። እልልልልልል ብለንም ቀወጥነው። ተነሣ ዐማራ ተነሣም ብለን ዘመርን። ምድር ቁና ሆነች። ዓለሙ ሁሉ ዋይ ዋይ አለ። የአውሮጳ ኅብረት ደንግጦ በአማርኛ መግለጫ ሰጠ፣ የዓለም መገናኛ ብዙሃን “በእውነት ዐማራ ተነሥቷል” ብለው በፊት ገጻቸው ጻፉ፣ ሰበር ዜናም በረከተ። አዎ ዐማራ ተነሥቷል። ሰባሪዎችን ሊሰብር ተነሥቷል። ይሄ ደግሞ የጫወታው ሕግ ነው።

“…አሁን ዐማራው ዝም ብሎ ተቀምጧል። ጩጬዎቹ ዲጄዎች ናቸው ዐማራ ዐማራ ሲሉ የሚውሉ የሚያድሩት። ያውም በአማርኛ። መሀመድ ሀሰን እንደሚለው ከኦሮሞ ዲጄዎች ወገን፣ ሕዝቅኤል ጋቢሳ፣ ሽመልስ አብዲሳ፣ ፀጋዬ አራርሳ፣ ጃዋር መሃመድ፣ ኢታና ሀብቴ፣ ግርማ ጉተማ፣ በቀለ ገሪባ፣ ኦነግ፣ ኦፌኮ፣ ኦህዴድ፣ ኦነግ ሸኔ፣ ኦነግ ሽሜ፣ ፕሮፍ መራራ፣ አቶ አሬራ ሁሉ ዐማራ ዐማራ ይሉ ገቡ። ከትግሬ ዲጄዎች በኩልም፣ እነ ቴዎድሮስ ርእዮት፣ እነ ዳንኤል ብርሃነ፣ ፍፁም ብርሃነ፣ አሉላ ሰለሞን፣ ዘራይ ኃይለማርያም፣ ስታሊን ገረሥላሴ፣ ሰናይት መብራቱ፣ ደረጺዮን፣ ሸዊት፣ ትርሃስ ሁሉም ዐማራ፣ ዐማራ፣ ዐማራ። ወዮ ወዮ ወዮ።

“…ከአዲስ አበባ ስዩም ተሾመ፣ ከአማሪካ ኤርሚያስ ለገሰ ዋቅጅራ፣ ከአውሮጳ ሞገስ ዘውዱ፣ እያስፔድ ተስፋዬ (ዳግማዊ ዋለልኝ) የወሃቢ እስላሙ ኢሳቅ እሸቱ፣ ስልጤው ሙጂብ አሚኖ ኧረ ማን ቀረ ናትናኤል መኮንን (አንደግመውም ወይ) ውብሸት ታዬ፣ የከሸፈው ፓስተር መሃል ሜዳ፣ ኮሮና ዳዊት፣ ኮሌራ መስፍን ፈይሳ፣ ዮኒ መጋኛ(ፆታዬን እቀይራለሁ) ደሩ ዘሀረሩ እንኳ ሲፎግር ነው። ሲያጃኩባቸው። ምድረ ጥቃቀን እና አነስተኛ በሙሉ ይኸው አሁንም ገብታችሁ እዩአቸው ዐማራ፣ ፋኖ፣ ፋኖ፣ ፋኖ እያሉ ነው። TMH, KMH, ZARA, TG, OMN ሁላቸውም የኢትዮጵያ ትንሣኤ ጌታቸውን፣ አለቃቸውን፣ ቀለም በጥብጦ፣ ፊደል ቀርጾ፣ ያስተማራቸውን የቀለም አባታቸውን በድንጋጤ፣ በፍርሃት፣ በመራድ ስሙን በመጥራት ላይ ይገኛሉ።

“…ጉደኛው ዐማራ ውሻው ዳንኤል ክብረት የሰደበው መስሎት ጃውሳ ቢለው ጭራሽ እኔ ጃውሳው ብሎ ፉከራ ገባ። ትግሬ እኮ ጁንታ ለምን እባላለሁ በፕሪቶሪያው ስምምነት ላይ ስሙ ይነሣልኝ ብሎ እያለቀሰ ነው። ዐማራው ግን ይገርማል። የጠላት ርግማን ምርቃት የሚያደርግ፣ ስድቡን እንደ ቅቤ የሚጠጣ፣ ነፍጠኛ ሲሉት አቤት ጠራችሁኝ ብሎ የሚያስደነብር፣ ጃውሳ ሲሉት አቤት ስሜ ነው የሚል፣ ወራሪ ሲሉት፣ ሰፋሪ ሲሉት ዘመሚት ይውረርህ፣ አጋንንት ይስፈርብህ ብሎ የሚመልስ። ጉድ እኮ ነው። አቢይ አሕመድ ትንፍሽ የለም። ትግሬ ላይ አፉን እንደከፈተው ዐማራ ላይ ዝም፣ ጭጭ፣ ደግሞስ የዐማራ ሴት ጭን ውስጥ ገብቶ ዓለሙን እየቀጨ እንዴት ዐማራን እንደ ትግሬ ያበሻቅጠው። ሃኣ…? ትላለህ አባቴ…

“…ላታመልጪኝ አታሩጪኝ አለች መሠረት ደፋር ኬኒያዊቷን አትሌት። ኢንዴዣ ኖ።

• ድርጅቱ ዘመዴ ነኝ አሸበርቲው።

Filed in: Amharic