>

ሊቀ ሣጥናኤል ሳይቀር የሚቀናበት የኦሮሙማ ጥጋብ ይሄን ይመስላል!! (ዳግማዊ ጉዱ ካሣ)

ሊቀ ሣጥናኤል ሳይቀር የሚቀናበት የኦሮሙማ ጥጋብ ይሄን ይመስላል!!

ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

የደብረ ታቦርን ከንቲባ ኦሮሙማዎች ለምን እንዳፈኑት  አሁን ተረዳሁ፡፡ “ይቅርታ እንጠይቅና ከሸሸን ሕዝብ ጋር እንታረቅ” በማለቱ ነው አሉ ያፈኑት፡፡ እንታረቅ ማለት ሲያሳፍንና ሲያስገድል ይታያችሁ እንግዲህ፡፡ እኔም እላለሁ – “እንዴት አደራችሁ” ማለት በኦሮሙማ ያሳፍናል፤ ያስገድላልም፡፡ ምክንያቱም “አሃ! ‘እንዴት አደራችሁ’ ያለው ደህና ማደራችንን ለማወቅ ሣይሆን ደህና ማደራችን አበሣጭቶት ነው” የሚል የተጣመመ ፍቺ ያሰጠዋልና፡፡ ከኦሮሙማ ጋር በፍጹም ተግባብቶ አንድ ላይ መኖር እንደማይቻል ግልጽ ሆኗል፡፡ አክራሪ ኦሮሙማዎች የሚናገሯቸውን የአደባባይ ዲስኩሮችና የአማራን እናጥፋ ቅስቀሣዎች ከሰማንማ ልናብድ ሁሉ እንችላለን፡፡ የሚገርሙ ፍጡራን፡፡ 

ምሣሌ ካስፈለገ፥ በአንዱ ጀማሪ አርቲስታቸው ከአዲስ አበባ ውጣልኝ የሚለውን ዘፈን አዳምጥ፡፡ ብርሃነ መስቀል አበበ ሰኒ ሰሞኑን “አማራ ኦሮምኛ ካልተናገረ ምኑን ኢትዮጵያዊ ሆነው” ብሎ ጎጃምንና ጎንደርን በተለይ ከኢትዮጵያ የሠረዘበትን ንግግሩን አዳምጥ፡፡ አንድ ጎልማሣ አክራሪ ኦሮሞ ደግሞ “አማራ ያለውን ሁሉ በአንድና ሁለት ዓመት ውስጥ ሸጦ ወይ ለውጦ በልቶ ይጨርስ፣ ከዚያ ያለፈ ዕድሜ አንሰጠውም፤ የአንድን ኦሮሞ ነፍስ በአንድ ሽህ አማራ ነፍስ እየለወጥን አማራን በአጭር ጊዜ ከምድረ ገጽ እናጠፋለን” ሲል በድፍረት የተናገረውን አዳምጥ፡፡ የአቢይንና የሽመልስን የዘወትር “አማራን እንሰባብራለን” ንግግርም ደርብበት፡፡ እነዚህ ሰዎች ግዴላችሁም ለይቶላቸው አብደዋል፡፡ 

በሌሎች ክልሎች ይኖር የነበረውን አማራ በመግደልም በማፈናቀልም ከየአካባቢው ጠራርገው እንደጨረሱ የሚያምኑት ኦሮሙማዎች አሁን በጃቸው ባስገቡት የሀገር መከላከያና የማይነጥፍ የሀገር ሀብት በመታበይ የአማራው ሣሎንና ማጀት(ጓዳ) ድረስ ዘልቀው በመግባት እሱንም ቤተሰቡንም እየደፈሩ፣ እየገደሉ፣ ብልት እየሰለቡ፣ ሀብት ንብረቱን እየዘረፉና እያወደሙ … ይገኛሉ፡፡ ትንሽ ሰው አይጥገብ፡፡ ትንሽ ሰው መኖር ከሚያስችለው አነስተኛ ግብኣት በስተቀር ምንም ዓይነት መልካም ነገር አያግኝ፡፡ ትንሽ ሰው ወደሀብትና ሥልጣን አይጠጋ፡፡ ትንሽ ሰው አግኝቶትና አይቶት የማያውቀውን ነገር ካገኘ ምን ሊሠራ እንደሚችል ለመረዳት ኦነግ/ኦህዲድን ማየት ብቻውን በቂ ነው፡፡ 

አማራው በኦነግ ፍዳውን አዬ፡፡ በዚያም ሳቢያ አማራው “እካብ ላይ ብሠራ እባቡ መከራ፤ እዛፍ ላይ ብሠራ አሞራው መከራ፤ የት ውዬ የት ልደር” እንዳለችው የጎንደሯ ወፍ ሆነ፡፡ በዚህን ጊዜ ነው እንግዲህ አማራው ላይመለስ ቆርጦ የተነሣው፡፡ መዳረሻው ደግሞ የጥፋቱ ድግስ መጠንሰሻው አዲስ አበባ አራት ኪሎ ቤተ መንግሥት ብቻ እንዳይሆን የኦሮሙማው ጥጋብ ወለድ ዕብሪት አማራው ከጎሬና ከባሌ የኬንያ ጠረፍ ወዲህ እንዳይመለስ ያስገድደዋል፡፡ እንግዲህ አክራሪዎች ሆይ! የተነሣባችሁ አማራ ላይ የፈጸማችሁትና እየፈጸማችሁት ያለው ዘግናኝ ግፍ ብቻ ሣይሆን የምሕረትም የበቀልም አምላክ የሆነው ኅያው እግዚአብሔርም ነውና መጪዋን ጊዜ ቻል አድርጓት፡፡ አዲስ ነገር አትጠብቁ – የዘራችሁትን ብቻ ነው የምታፍሱት፤ ሊያውም ታይቶ በማያውቅ አዲስ እንቅብና ቁና፡፡

በዚህ አጋጣሚ የዘር ሐረግን መሠረት አድርጋችሁ የአማራውን የነፃነት ትግል የሚያጠለሽ ስድብ ለምትሳደቡ ሁሉ አጭር መልእክት አለኝ – እርግጥ ነው ተሳዳቢዎች ሁሉ አማራ ናቸው ብሎ መደምደም አይቻልም፤ ምክንያቱም በአማራ ስም ጥላቻን የሚቆሰቁስና የሚያራግብ ትግሬም ሆነ ኦሮሞ ወይንም ተቀጣሪ የሌላ ጎሣና ነገድ አባል አይጠፋምና፡፡ መታወቅ ያለበት ትልቁ እውነት ግን በማንም ይሁን በማን በዘር መሣደብ(መሰዳደብ) በርግጥም አሣፋሪና አስነዋሪ መሆኑን ነው፡፡ ስድብ በመሠረቱ ይቅርታ ይደረግልኝና የቀነጨረ ወይም ማሰብ ያቆመ አእምሮ ውጤት ነው፡፡ በአማራነት ማንም ሊሰደብ እንደማይፈልግ ሁሉ አማራ ነኝ የሚልም ዘርን ተመርኩዞ ማንንም መሣደብ የለበትም፡፡ በልጁ፣ በሚስቱ፣ በአባት ወይ በእናቱ፣ በጋብቻ በአምቻ በተሳሰረና በተዋሃደ ማኅበረሰብ ውስጥ የዘር ሐረግን መሠረት አድርጎ መወራረፍ ትንሽነትን ከመግለጽ ባለፈ ወዳጅ ዘመድን ማስከፋትና በሚደርስብን ግፍና በደል የሚያዝንልን ወገን እንዳይኖር ሰዎችን መግፋት ነው፡፡

ስለዚህ የመሸታ ቤት ንቁሪያዎች በዚያው ይቅሩ፡፡ አንድ ሰው በሚያሣየው አፍ እላፊ 60 እና 70 ሚሊዮን አማራ አይወቀስ፡፡ የሰማ ይስማ፤ ያልሰማን ልብ ይስጠው፡፡

ትንንሽ ነገር ደግሞ አንመኝ፡፡ አሁን ትግሉ ስለአንድ ክልል መሿሿም አይደለም፡፡ ሀገርን የማዳን ትግል ነው፡፡ የአማራንና መሠል ኢትዮጵያውያን ዜጎችን ከሰው በላው ጭራቅ ኦሮሙማ የመታደግ ትግል ነው የተጀመረው፡፡ እንጂ ዘመነን ወይ ክርስቲያንን ወይ እስክንድርን በውሽልሽል የአቢይ ሠራሽ ክልላዊ ወንበር ላይ ለላንቲካው የመጎለት ጉዳይ አይደለም፡፡ ሰፋ አድርገን እናስብ ወጎኖች! አማራ በድርድርና በሽምግልና የሚወገድ ችግር ውስጥ አልገባምና ይህን መሰሉን የጠላት ወሬና ሽንገላ መስማትና ማመን ለአማራ ዕልቂት መሣሪያ መሆን ነው፡፡ የአማራም ሆነ የኢትዮጵያ ብቸኛ መዳኛ የኦሮሙማና የትግሩማ ዲያቢሎሣዊ የዘረኝነት ልክፍት ከምድረ ገጽ መጥፋት ነው፡፡ ከዚያ በመለስ ያለው የመፍትሔ ሃሳብ ሁሉ ጠላቶች ስሊያቸውን ተይዘው በሚጨነቁ ጊዜ፣ ጊዜ እስኪያገኙና ኃይልና እስትንፋስ እስኪያሰባስቡ ድረስ የሚያንገዳግዳቸው የመቆያ ሥልት ነው፡፡ እባብ በምንም ዓይነት ሁኔታ ተፈጥሮውን ለውጦ ዕርግብ ሊሆን አይችልም፡፡ ጅብና ዓሣማም ልክ እንደዚያው፡፡ ኦሮሙማ በተለይ ለአማራው ያለው ጥላቻ ሥር የሰደደ እንደመሆኑ በተጀመረው የነጻነት ትግል ጥግ እንዲይዝ ካልተደረገ በስተቀር ሌላው ይቅርና አዲስ አበባና በዙሪያዋ የሚኖረው አማራ ከስድስት ወር ያለፈ የቆይታ ዕድሜ አይኖረውም፡፡ እንደሚታዬው በአሁኑ ወቅት የአማራና የኢትዮጵያ ታሪክ አካል ናቸው የተባሉ ሕንጻዎችና ቅርሶች እየፈራረሱ ነው፤ ማዘጋጃ ፊት ለፊት ያለውን የአራዳ ሕንጻና ሸበሌ ሆቴል ፊት ለፊት የነበረውን የአነስተኛና ጥቃቅን ኢንዲስትሪ መንደር መመልከት ትችላለህ፡፡ ፍርስርሳቸው እየወጣ ለነአዋሽ ባንክና መሰል ኦሮሙማዊ ተቋማት እየታደሉ መሆኑ ይነገራል፡፡ ሀገር አለች የምንለው በወሬና በታሪክ ብቻ ነው ጎበዝ፡፡ … ሕዝቡ ግን ቀልዱን እንደቀጠለ ነው፡፡ ይገርማል፡፡ አማራ ሎተሪ አዙሮና በባጃጅና በሞተር ሣይክል ተሯሩጦ የዕለት ጉርሱን ማግኘት አይችልም፤ አማራ በአርከበ ሱቆችና በሸራና በላስቲክ ቤቶች ሽሮና ቆሎ ሸጦ እስትንፋሱን ማቆየት አይችልም፤ አማራ የሚጣልበት ግብርና ቀረጥ ምን ያህል ደም የሚያስቀምጥ እንደሆነ የሚታወቅ ነው፡፡ አማራ ልመናና ዘበኝነትም ተከልክሎ ምን ያህል ስቃይ ውስጥ እንደሚገኝ እናውቃለን፡፡ … ዝርዝሩ ብዙ ነው፡፡ ዋናው ግን ፋኖ በርታ፡፡ እንደሰው ተቆጥረን በገዛ ሀገራችን ተከብረን መኖር የምንናፍቅ ዜጎች ሁሉ ከፋኖ ጎን ቆመን የማይቀረውን የትንሣኤያችንን ዘመን በጋራ እናምጣ፡፡ ፋኖ ብቻውን ዕዳ የለበትም፡፡ ዛሬ ሚሊዮነር የሆንክ አማራ የተዘባነነ ኑሮ የምትኖር ከመሰለህ ስህተት ነው፤ ተራህ እስኪደርስ እንጂ አንተም የኦሮሙማው ሰለባ ሆነህ ነገ ጧት ማበድህ አይቀርም፤ መገደልህም፡፡ ይህን የምለው ብዙ ነገሮችን ስለምረዳና በርካታ ገልቱዎች ዛሬ የሚሆኑትን ስለምገነዘብ ነው፡፡ …

Filed in: Amharic