>
5:14 pm - Friday April 30, 3086

ያማራ የሕልውና ችግር ሁለቱ ምንጮችና ዘላቂ መፍትሔው

ያማራ የሕልውና ችግር ሁለቱ ምንጮችና ዘላቂ መፍት

ያማራን ሕልውና እጅጉን እየተፈታተኑ ያሉት ጭራቅ አሕመድና መሰሎቹ የበሽታ ምልክቶች እንጅ በሽቶች አይደሉም።   በሽታወቹ ደግሞ ጭራቅ አሕመድንና መሰሎቹን በላዔ አማራወች ያፈለቁት ሁለቱ ፀራማራ ምንጮች ናቸው።  ስለዚህም ያማራ ሕዝብ ሕልውናውን ለዘለቄታው ማረጋገጥ የሚችለው እነዚህን ሁለት ፀራማራ ምንጮች ለዘላለም ካደረቀና ካደረቀ ብቻ ነው።  ያማራ ሕዝብ ለዘላለም ሊያደርቃቸው የሚገባ ጭራቅ አሕመድንና መሰሉቹን ያፈለቁት ሁለቱ ፀራማራ ምንጮች ደግሞ የሰውና የቦታ ስያሜወችን የተመለከቱ ናቸው።  

ሰብዓዊነት የሚባል ምናምኒትም ስላልፈጠረበት ከእንስሳ ሊቆጠር የሚችለው አረመኔው የገዳ ጨፍጫፊ ሠራዊት በግራኝ አሕመድ ጦርነት የተዳከመውን ያማራን ሕዝብ እየጨፈጨፈ ባማራ ግዛት ላይ ሲስፋፋ፣ ከጭፍጨፋው የተረፉትን አማሮች በሞጋሳና በጉዲፈቻ ዘዴ የኦሮሞ ስም እየለጠፈ ኦሮሞ ናቸሁ አላቸው።  የተስፋፋባቸውን ያማራ ግዛቶች ደግሞ በነገዱና በጎሳው እየሰየመ የኦሮሞ ናቸው አላቸው።  ያማራ የሕልውና ችግር የሚመነጨው ከነዚህ ሁለት ምንጮች ነው።

አያቶቻችን ከለማበት የተጋባበት እንዲሉ፣ የኦሮሞ ነጻነት ታጋዮች ነን በማለት ዛሬ ላይ ያማራን ሕዝብ ለማጥፋት ቆርጠው የተነሱት እውነተኞቹ የቦረና ኦሮሞወች ሳይሆኑ፣ ኦሮሞነት በስም እንጅ በደም የሌለባቸው ጭራቅ አሕመድ፣ ለማ መገርሳ፣ ሽመልስ አብዲሳ፣ ዳውድ ኢብሳ፣ መራራ ጉዲና፣ በቀለ ገርባ፣ ጃዋር ሙሐመድና መሰሎቻቸው ናቸው።  እነዚህ የቁጩ ኦሮሞወች ያማራን ሕዝብ ለማጥፋት ቆርጠው የተነሱት ደግሞ የኦሮሞ ያልሆኑትን ቦታወች በኦሮሞኛ ስለተሰየሙ ብቻ የኦሮሞና የኦሮሞ ብቻ ናቸው በማለት ነው።   

የቦታወችን ስያሜወች በተመለከተ መፍትሔው ላማራ የሕልውና ትግል ያጭር ጊዜ ሥራ ነው።  ያማራ ሕዝብ በመራራ ትግሉ የጭራቅ አሕመድን ኦነጋዊ መንግስት አስወግዶ ጭራቅ አሕመድንና ግብራበሮቹን (በተለይም ደግሞ የአብን፣ የኢዜማና እና የብአዴን ግብራበሮቹን) ማስተማሪያ በሚሆን መንገድ አይቀጡ ቅጣት ከቀጣ በኋላ የጦቢያን ሐገረ መንግሥት እንደገና ሲያቋቁም፣ ተስፋፊው የገዳ ሠራዊት ያወጣቸውን የመስፋፋት ስሞች (ውሎ፣ ወራኢሉ፣ ጉለሌ፣ ሰላሌ ወዘተ ) አንዳችውም ሳይቀሩ ሁሉንም በሕጋዊ መንገድ ላንዴና ለመጨራሻ ጊዜ ማጥፋትና ሁሉንም ቦታወች በቀድሞ ስማቸው መሰየም አለበት።  ለምሳሌ ያህል ጨፍጫፊው የገዳ ሠራዊት ባወጣለት የጭፍጨፋ ስሙ ወሎ የሚባለውን ቤታማራን ወሎ ብሎ በኦፊሴል (officially) መጥራት በጭፍጨፋ መስፋፋትን ከመደገፍ የሚያስቆጥር ከባድ ወንጀል መሆንና ከባድ ቀጣት ማስከትል አለበት።  አልኦፌሴል (non-officially ማለትም ባዘቦት ንግግር ላይ) ቤታማራን ወሎ ብሎ መጥራት ደግሞ ተናጋሪውን ማሳፈርና ማሽማቅቅ አለበት።  

የሰወችን ስያሜወች በተመለከተ ግን መፍትሔው ላማራ የሕልውና ትግል የመቶ ዓመት ሥራ ነው።  ያማራ ሕዝብ የጭራቅ አሕመድን ኦነጋዊ መንግሥት ካስወገደ በኋላ ሕልውናውን በተመለከት ትልቁ ሥራው መሆን ያለበት የሚከተለው ነው። እሱም ኦሮሞ ነው ከሚባለው ሰፊ ሕዝብ ውስጥ ከዘጠና በመቶው በላይ ኦሮሞ እንዳልሆነ፣ የኦሮሞ ስም ስለተለጠፋባቸው ብቻ ኦሮሞ ነን ብለው እንዲያምኑ የተደረጉትን ሚሊዮኖች ወደ እውነተኛ ማንነታቸው በራሳቸው ፈቃድ እንዲመለሱና፣ ያለስማቸው ስም የሰጣቸውን የኦሮሙማ አስተሳሰብ እንዲጸየፉትና በጽኑ እንዲዋጉት ማድረግ ነው።  ይህ ማድረግ ደግሞ እያንዳንዱን አዲስ ትውልድ በከፍተኛ ትግስትና ትጋት ሳያሰልሱ ማስተማርን የሚጠይቅ የዘመናት ፕሮጀክት ነው።  

አጼ ሚኒሊክ ያማራን ግዛቶች እንዳስመልሱ፣ አረመኔው የገዳ ሠራዊት የፈጠራቸውን የሰውና የቦታ የጭፍጨፋ ስሞች በቀላሉ ማጥፋት ይችሉ ነበር።  ይህን አድርገው ቢሆን ኖሮ ደግሞ ወሎ፣ ወረኢሉ፣ ጉለሌ፣ ሰላሌ የሚባሉ፣ አሁን ላይ አማራን ለመጨፍጨፍ የሚያገለግሉ ቃሎች ከመቶ ዓምታት በፊት ድምጥማጣችው በጠፋ ነበር።  ለማ መገርሳና ሽመልስ አብዲሳ የሚባሉ፣ ኦሮሞ ሳይሆኑ ከእውነተኛ ኦሮሞወች በላይ ኦሮሞ ነን የሚሉ፣ ባማራ ጥላቻ ያበዱ የማንነት በሽተኞች ባልተፈጠሩ ነበር።  

አጼ ምኒሊክ ግን በቀላሉ ማድረግ ይችሉት የነበረውን ባንድም በሌላም ምክኒያት (ምናልባትም ደግሞ የጨፍጫፊን ስያሜ መቀበል ለጨፍጫፊ የልብ ልብ ከመስጠት ሊቆጠር እንደሚችል ስላልታያቸው) ሳያደርጉት ቀሩ።  ስለዚህም ያማራ ሕዝብ ሕልውናውን ለዘላለም ማረጋገጥ የሚችለው፣ አጼ ምኒሊክ የጀመሩትን መንገድ በመጨረስ፣ ጨፍጫፊው የፈጠራቸውን የጭፍጨፋ ስሞች አንዳቸውም ሳይቀሩ ሁሉንም ለዘላለም በማጥፋት ብቻ ነው።  ይህን ሲያደርግ የኦሮሙማ ምንጭ ለዘላለሙ ስለሚደርቅ፣ ኦነግና መሰሎቹ በሂደት ይከስማሉ፣ ያማራ ሕዝብ የሕልውና ችግርም መችም እንዳይመለስ ሁኖ ከምንጩ ይወገዳል።   ነገር ከፍንጩ፣ ውሃ ከምንጩ።      

ያማራ ሐለወት አደጋ ላይ ወድቆ፣ እየተቀበረ በማሽን ተዝቆ፣

ጽንፈኛ ኦሮሞ ጉቱም ሆነ ዋቆ፣ ይቀየማል ብሎ ማውራት ተጠንቅቆ

ትርፉ መዋረድ ነው ፈሪ አስብሎ አስንቆ፡፡

ኦነግ ቄሮን ሲግት ያኖሌን ፈጠራ፣ የሉባን ጭፍጨፋ ማለት አይወራ፣

ሜዳውን በመተው ላባዱላ ሤራ፣ ትርፉ ማባባስ ነው ያማራን መከራ፡፡

ሱማሌ በጅራፍ ያስወጣው ከኦሞ፣ የሉባው ሠራዊት የገዳው ኦሮሞ፣ 

ሐበሻን ሲያገኘው በግራኝ ተዳክሞ፣ ጨለማ ተላብሶ እያረደ አጋድሞ፣

ባበሻ ምድር ላይ በያቅጣጫው ተሞ፣ የተንሰራፋ ነው እንደ አረማሞ፡፡

በጦቢያ ምድር ላይ ከጣና እስከ ጫሞ፣ በኦሮምኛ ቃል ያለ ተሰይሞ

ከመስፋፋት በፊት ሁሉም አስቀድሞ፣ አይደለም ኦሮሞ ወይም የኦሮሞ፡፡

በስሙ ኦሮሞ ከሆነው ሕዝብ ላይ፣ ዘጠና በመቶ ወይም ከዚያ በላይ

በደሙ ያይደለ ብሔሩን የረሳ፣ ወይ ጉዲፈቻ ነው አለያም ሞጋሳ።

በስሙ ቢባልም ኤጀርሳ፣ ኤለሞ፣ በደሙ ያልሆነ ሐበሻና ጋሞ

እንዲሁም ወላይታ፣ ሐድያ፣ ሲዳሞ፣ እስኪ ተናገሩ የቱ ነው ኦሮሞ?

ሽመልስ አብዲሳ ያልተገራው ስዱ፣ ነፍጠኛን ሰበርነው ሲል እንደልማዱ፣

የቦረና ውልዱ ሳለ የምጣዱ፣ አትንጣጣ በሉት አንተ የሰፌዱ፡፡

ኦሮሞን አይተነው በዚህ ረገድ ዓይን፣ ሕዝቡን ስንመዝነው በትክክል ሚዛን፣

መሆን ይቅርና የጦቢያ ብዙሃን፣ እጅግ ያነሰ ነው ከሁሉም ሕዳጣን፡፡

ኬኛ፣ ኬኛ እያለ ራሱን በማግለል፣ ከጦቢያ ብሔሮች እኔ በመነጠል

ካልፈጠርኩኝ ካለ የኦሮሞ ክልል፣ ባሌም አይገባው ላሥር ሳይከፈል፡፡

መስፍን አረጋ

mesfin.arega@gmail.com

Filed in: Amharic