>

ስለወደቀው የጋዜጠኝነት ክብር!

ስለወደቀው የጋዜጠኝነት ክብር!

ሢሣይነሽ መንግሥቴ

ጋዜጠኛው. . .ጋዜጠኛው

                  ጋዜጠኛው

       ኑሮው ልቤን ነካው

      – ድምጻዊ ቴዎድሮስ ሞሲሳ

ከሰሞኑ በአቶ ጸጋዬ ደበበ ባለቤትነትየሚተዳደረው ሱፐር ደብልጄኔራልትሬዲንግ ስም በመገናኛ ብዙሃን አየር ላይናኝቶ ነበርኩባንያው ከፈጸማቸው የተለያዩየመብት ጥሰቶች እና አስጸያፊ ድርጊቶች ባለፈብዙዎች ትኩረት የሰጡት እነዚህን ተግባራትበጽኑለማስተባበል የገንዘብ እና የሃሳብስምሪት ተላልፎላቸው በተንቀሳቀሱጋዜጠኞች ላይ ነበርጉዳዩን በተመለከተከመነሻው አንስቶ በትኩረት እየተከታተለሲዘግብ የቆየው ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረትጋዜጠኞቹን በ”አልጀዚራእና በ”ኩኪስምድብ ከፍሎ ሰይሟቸው እንደነበርየምታስታውሱ ይመስለኛልበራሱ ይፋዊየፌስቡክ ገጽ ላይ የሁለቱ የጋዜጠኞች ምድቦችምንነት ከዚህ እንደሚከተለው አብራርቶትነበር

አልጀዚራ:

በዚህ ምድብ ያሉት ልክ እንደ አልጀዚራጋዜጠኞች ትልልቅ የቪድዮ እና የፎቶካሜራዎችን ተሸክመው በጋዜጣዊመግለጫዎች ድግስ ኮንሰርት ኮንፈረንስየዝነኞች ቤቢ ሻወር ሰርግወዘተ በመሄድምስል የሚቀርፁ በመምሰል ይገኛሉ ብዙዎቹግን ቪድዮ መቅረፅ የማይችሉ ካሜራቸውንየውጭ በር ማለፊያ አርገው የሚጠቀሙናቸው ከዛም የተገኘውን ምግብም ሆነ የኪስአበል በመጠቀም ኑራቸውን ይገፋሉ

ኩኪስ:

እነዚህኛዎቹ ቁጥራቸው በዛ ያለ ሲሆን አዲስአበባ ውስጥም ሆነ ክፍለ ሀገር ዝግጅት አለሲባል በፍጥነት በመገኘት ይታወቃሉ ኩኪሶችየሚሰሩበት የሚድያ ተቋም የላቸውምስራቸው የሚሰጣቸውን መረጃ በግል የፌስቡክገፃቸው ማጋራት ነው የጋዜጠኛ መለያየሆኑትን እንዴት? መቼ? ለምን? የሚሉጥያቄዎችን አይጠይቁም ተፅፎየሚሰጣቸውን ጋዜጣዊ መግለጫ (press release) በቀጥታ ያጋራሉ የኪስ አበል እናኩኪስ/ድግስ ይቋደሳሉ

በርግጥምየዛሬ ሳምንት ዓለምገና የዘመቱትጋዜጠኞች በሁለቱም ምድብ ውስጥየሚቀመጡ መሆናቸው አያጠራጥርምእኔምከጋዜጠኞቹ መካከል አንዷ ነኝና ያለምንምርህራሄ ራሴን በሁለቱም ምድብ ውስጥ ነውየማስቀምጠውምክንያቱም መጀመሪያ ዘገባለመስራት እንደቅድመ ሁኔታ የምመለከተውጉዳይ ውሎ አበል እና ምግብ ነውዝግጅቱጠቀም ያለውሎ አበል ካለውኪሴም ሆነጥርሴ ፈገግ እያሉ ዜናውን አሽሞንሙኜእሰራዋለሁነገር ግን የረባ ምሳ ወይም ኮክቴልየሌለው ዝግጅት ላይ ለዘገባ ከተመደብኩዜናውን አኮስምኜ ለአንባቢ አቀርበዋለሁአንባቢዎቼ ይህ አካሄዴ በዋናነት ራሴውድህነት ሁኔታ (የገንዘብ ድህነት) ጋርእንደሚያያዝ ልታውቁልኝ ይገባል

የዛሬው ጽሑፌን ዋና ትኩረትጋዜጠኝነት እናድሕነትበሚል ርዕስ ስር ለመቀንበብ ነበር ዋናዓላማዬይህ ርዕስ ከሚፈልገው ሰፊ የንባብአቅም እና ጊዜ የተነሳ ሃሳቤን ወደ ግላዊልምዶች እንድቀይር ተገደድኩ ጽሑፌ የሁለቱምድብተኛ ጋዜጠኞ ነባራዊ ሁኔታ ምንእንደሚመስል ይዳስሳል

ከሁሉም በላይየዓለምገና ትዝብቴየተሰኘውየጉዞ ማስታወሻዬ የራሳቸውን ጎራ ቀልሰውበሚንቀሳቀሱጋዜጠኞችዘንድ አቧራማስነሳቱን እዚህ ላይ ለመጥቀስ እወድዳለሁየአቧራው መቡነን አንዳንድ ጉዳዩ በቀጥታየማይመለከታቸውን ዜጎች እያሰቃየ እንደሚገኝየተለያዩ መረጃዎች ደርሰውኛልእንግዲህመራር ሃቅ ሲወጣተጓዳኝ እና አላስፈላጊጉዳት ለሚገጥማቸው ሰዎች ከወዲሁ ሃዘኔንእየገለጥኩወደ ዋና ነጥቤ ልመለስ

እኔ ወደ ጋዜጠኝነት ሞያ ከገባሁ ወደ አስርትዓመታት ገደማ እየተጠጋሁ ነውበዚህየጋዜጠኝነት ሕይወቴ ክፉንም ደጉንምተመልክቼአለሁየሞያተኞቹን ደግ እና ዕኩይተግባራት ወይም ባሕርያት ታዝቤያለሁከሁሉም የሚደንቀኝ ነገር አንዳችም ሞያዊአቅም ሳይኖራቸው የጋዜጠኝነት መድረኩንያጣበቡ ሰዎች መብዛታቸው ነውበተቃራኒው ደግሞየሞያው ፍሬ ነገርገብቷቸው ለመስራት እየሞከሩግና በገንዘብዕጥረት የሚሰቃዩ በርካታ ጋዜጠኞች አሉ

በኢትዮጵያ ከመንግስት ቀጥተኛ ቁጥጥርውጪ ባሉ የግል መገናኛ ብዙሃን ተቀጥረውየሚሰሩ ጋዜጠኞች በጋራ የሚያሰቃያቸውአንዳች ሕመም አለእርሱምድህነትይባላልበተቋማቸው የሚከፈላቸው ገንዘብ ከቤትኪራይ እና ከዕለት ጉርስ ባለፈሌላ የተሻለ ነገርየሚያሰራ አይደለምይህም የደመወዝዝቅተኝነት ወደአልጀዚራ”ነት ይገፋፋቸዋልተቋማቸው አሰማርቷቸው ከሚሄዱበትዝግጅት ሌላራሳቸውን ደብቀውባልተጠሩበት ድግስ ላይ ድንኳን ሰባሪ ሆነውይመጣሉችግር የወለደው ዕርምጃ!

ሌሎቹከላይ ጥቂቱ የጠቀስኳቸውበድሮ ዓመታት በመጽሔቶችበጋዜጦች እናበሌሎች የመገናኛ ብዙሃን ዘዴዎች ላይተቀጥረው ሲሰሩ ወይም ተቋማቱንበባለቤትነት ሲያስተዳድሩ የነበሩጋዜጠኞች”፣ አንድ የፌስቡክ ገጽ ወይም የዩቲዩብ ቻናልከግለሰብ በመግዛትአዲስ የ”ሚዲያስምበመሰየም የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦች ናቸውእነዚህ ግለሰቦች በየጋዜጣዊ መግለጫውበየሁነቱ የሚገኙ በመሆናቸው በጣምይታወቃሉ (በዓለምገናው ጉዞ ላይ ተነሷቸውፎቶግራፎች ላይ ሰፊው የታዩት ናቸው)። ለእነርሱ ድንኳን መስበር የዕለት ተለት ገቢእንጂ ተጨማሪ ገንዘብ አይደለምየትኛውምዓይነት ሁነት ቢጠፋሕልውናቸው ያከትማልዕድሜ አይኖራቸውም

የሰዎቹን ስም አልጠራምነገር ግን በየሁነቱወይም በየጋዜጣዊ መግለጫውጠጋ ብለውቢሞክሩት የማይሰራ ማይክራፎን ከሎጎ (አርማ) ጋር አሰርተው ሲደቅኑ የሚያዩዋቸው ሰዎችያውቋቸዋልይህን ጽሑፍ ሲያነብቡ። “የማይሰራ ማይክራፎን?” በማለት የምትደነቁአንባቢዎቼ እንደምትኖሩ ርግጠኛ ነኝ

አትደነቁሌሎች የቴሌቪዥን ጣቢያዎችአርማዎቻቸውን ያነገቡ ማይክራፎኖችንስለሚይዙተዓማኒ ናቸውብለው ለሚያስቡለእነዚህ ሰዎችይህ የማጭበርበር ስራቸውየመጠቀ እና የተመሰጠረመስሎ ነውየሚታያቸውግና ማይክ ደቅነው የቀረጹትንዝግጅትም ሆነ ቃለ መጠይቅ በፌስቡክገጻቸው ወይም የዩቲዩብ ቻናላቸው ላይለተከታዮቻቸው ሲያጋሩ አንመለከትምለምን? “አልጀዚራስለሆኑ!

የሚያሳዝነው ነገር እነዚህን ሰዎች በአክብሮትጠርተው፣ “ሞቅ ያለውሎ አበል ከፍለውየሚጋብዟቸው መንግስታዊ እና የግል ተቋማትመኖራቸው ነውየየተቋማቱ የሕዝብግንኙነት ክፍሎ ስለእነዚህጋዜጠኞችምንነት እና ስራ ለማጣራት ጊዜ የላቸውምስራ በዝቶባቸው ሳይሆንከሰዎቹ ጋር የጥቅምሽርክና ስላላቸው ነውየሚኒስቴር መስሪያቤቶች የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊዎችን ልብይሏል!

ይግረማችሁና እነዚህ ሰዎች የዕዝ ማዕከልአላቸውማዕከሉ በትልቅ ሕንጻ ውስጥየሚገኝ ከመሰላችሁ ተሳስታችኋልበአንድየአዲስ አበባ ኮስማና ሰፈር ውስጥ ሚገኝአረቄ ቤት ግለሰቦቹ ተሰባስበው ከየመረጃምንጮቻቸው የመጡትን የ“ይዘገብልኝደብዳቤ ይከፋፈላሉየዓይኑ ቀለምያላማራቸው የሚመታ” (በሃሜት ስሙየሚጠፋ) ግለሰብ ካለወሬ ይቀመማልይሰራጫልበቀረው ጊዜ ደግሞሌሎችአጓጉል ተግባራት ወናሉ። (ለአንባቢክብር ስልድርጊቶቹን ከመጥቀስ እቆጠባለሁ!)

ጋዜጠኞቹን በአበል የሚያሰባስብ አንድ ግለሰብደግሞ አለላችሁስሙን አልጠቅስም ይህሰው ብዙ ዓይነት ማዕረግ አለውጋዜጠኛፕሮሞተርየማስታወቂያ ባለሞያብዙ ቅጽልስሞች አሉትበየጋዜጣዊ መግለጫውለሚመጡ ሪፖርተሮች የውሎ አበል መክፈልያለማመደውእርሱ ነውይባላልይህምከዘጠኝ ዓመታት በፊት ማለት ነውቀስ በቀስየክፍያ መጠኑን በማሳደግ ጋዜጠኞችንበቁጥጥሩ ስር ማዋል ችሏልይሁንናሰውዬው መሰረታዊ የጋዜጠኝነት ዕውቀትየሌለውምስኪንሰው ነውሆኖም ግንድፍረት ብቻ ነው እዚህ ደረጃ ያደረሰውኢትዮጵያ ውስጥ ድፍረት ወለድ ስራዎችበየጊዜያቱ የወለዱት ጥሩ ልጅ የላቸውምከብልሹነት በስተቀር!

እነዚህ የሙሉ ጊዜአልጀዚራእናኩኪስጋዜጠኞች የኢትዮጵያን የጋዜጠኝነት መድረክበአቅመ ቢስነታቸው ጥልቀት እየበከሉት ነውይህም ቢቀር እንኳጥያቄ የሚያነሱ እናከእነርሱ ቡድን ጠገግ የራቁ ጋዜጠኞችንጠልፈው ለመጣል ብሎም ለመስበርእየተንቀሳቀሱ ነውከኢትዮጵያ የመገናኛብዙሃን ባለስልጣን ሕጋዊ የዲጂታል ሚዲያፈቃድ ሳይኖራቸውየንግድ ፈቃድ እና የግብርመክፈያ ቁጥር (ቲን ነምበር / TIN Number) ሳያወጡ በሃሰተኛ ማሕተም እናየመገጣጠሚያ ደብዳቤ ብዙ ሺሕ ብሮችንወደ ሒሳብ ቁጥራቸው ገቢ የሚያደርጉናቸውእናምእስከ መቼ ነው ዝምየሚባሉት?

እነጳውሎስ ኞኞእነሙሉጌታ ሉሌእነበአሉግርማ ያቀኑት የጋዜጠኝነት ክብር ወደቀድሞው ስፍራ ለመመለስ ጊዜው መቼ ነው?

Filed in: Amharic