ሊነጋ ሲል ይጨልማል !!

ከድር ጠንክር  ከመርካቶ

ሰሞኑን ቴዲ አፍሮ ቀቀው አዲስ ዘፈን፤

እኛ የመርካቶ ልጆች ስምምነን !! ብለናል
እኛ የፒያሳ ልጆች ብልጭታ ነው !! ብለናል
እኛ የልደታ ልጆች ጽዮኝ ሙሽራዬ !! ብለናል
እኛ የካሳንቺስ ልጆች ታየን !! ብለናል
እኛ የቄራ ልጆች ጀምበር….ስትጠልቅ !! ብለናል
እኛ  የንፋስልክ ልጆች የአዞ እንባ !! ብለናል
ስደተኞ እህቶቻችን መሬማ !! እያሉ ያዜማሉ
መላው ኢትዮጵያዊ ዳስ ጣል !!! ብሏል
መላው አፍሪካዊ ኢቶሪካ !!! እያለ ያዜማል
መላው ዓለም ሙዚቃ የዓለም ቋንቋ ብሎለታል……….ወዘተ.

አለመታደል ሆኖ በበሉበት የሚጮሁና፤ አይምሯቸው በጮማ የተደፈነ፤ የሥነ ጥበብ*1 ምንነት፤የመረዳት አቅማቸው እጅግ የወረደ ከማለት በከፋ መልኩ፤ በእጅጉ የዘቀ ሰዎች፤ የቴዎድሮስ ካሳሁን (የቴዲ አፍሮን) ዘፈን፤ ሰዎች በነፃነት እንዳያዳምጡከልክለዋል ::

የዘፈን ዜማን በጆሮ ማንቆርቆር፤ ውበትን ማድነቅ፤ ስነ ጽሁፍን መመርመር፤ ለስነ ሥዕል ትኩረት መለገስ፤ በግጥም መደመምን፤ በፈጠራ የድርሰት ሥራ፤ (በሥዕላዊ ወይም ታሪካዊ ድርሰት)፤ ሃሳብን በሃሳብ እያሞሻለ፤ አይምሯቸውን በመሞረድ፤ ሰውጆች እራሳቸውን እንደሊፈጥ እንደሚች ገና አልተረዱም ::

ሰው በእህል ብቻ አይኖርም….. !!!  የሰውል ልጅ መንፈሱን እያስራበ፤ ሥጋውን ብቻ ለማደለብ፤ ክምር ያህል እየበላ፤ ሽንትቤት የሚሞላ እበት ለመጣል ብቻ አልተፈጠረም ::

በሥነ ጥበብ መንፈሱን መመገብና ማለምለም፤ የመፈጠሩ የመጀመሪያው ምእራፍ እንደመሆኑ ሁሉ፤ለመጨረሻው ግብተ መሬቱም መሸኛው ነው ::

ለስነ ጥበብ የአይምሯቸውን በር ዘግተው፤ በጨለማ ውስጥ መኖርን ለመረጡ የምንላቸው፤

ሥነጥበብ :

ብልጭታ ነው ! ጨለማን ቀዶ የሚፈነጥቅ ነቁጥ
ጮራ ነው ! ጨለማን ገፎ ምንነትንና ማንነትን የሚያሳይ
ንጋት ነው ! የወደፊት ተስፋን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ
ጎህ ነው !  የጨለማው ጊዜ አልፎ፤ ብሩህ ቀን እንደሚመጣ የሚያበስር
ውህደት ነው ! የሥጋንና የብስ ጥምረት ነጋሪ፤
የፀሐይ ነው ! ሰውነትን በሙቀት እንደ እጽዋት የሚያለመልም……. ::

ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ምሁራን ተብዬዎች ሁሉ : አጎንብሰው እንብርታቸውን ሲያስተናግዱ፤ ጭው ባለው በረሃ፤ እንደ መጥምቁ ዮሐንስ : ድምጹን ከፍ አድርጎ፤ በድፍረት ሃቁን የተናገረ፤ የጥበብ ባለሞያ ነው !!

ቴዎድሮስ ካሳሁን፤ 

ፍቅር ነው ! በጥላቻ ልቡ ያልጠቆረ፤
ሠላም ነው ! ጦርነትን ኮንኖ ለዜጎች በህይወት መኖር ጥብቅና የቆመ
አንድነት ነው ! በዘርና በጎሣ አጥር ተከልሎ ከመኖር፤ አብሮነትን የመረጠ
ድምፅ ነው ! የሁላችንን ጩኸት ከፍ አድርጎ ያሰማ
ነፃነት ነው ! አጎንብሰን በባርነት መኖርንእንድንጠየፍ የመከረ
ሠንደቅ ነው ! ለአረንጓዴ ቢጫና ቀይ ሠሰንረቅ አላማችን ዘብ እንድንቆም ያሳሰበ
ትሁት ነው ! ትንሽ ትልቅ፤ ድሃ ሃብታም ሳይል ለሁሉም የቆመ
ክብር ነው ! ኢትዮጵያን ዝቅ ብላ ሲያት ለክብሯ የተቆጨ
ትንቢት ነው ! መጭውን ጊዜ አመላካች
ተስፋ ነው ! የኢትዮጵያን ትንሳዜ ነጋሪ

ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) በኢትዮጵያ የፈጠራ ሥራ ሞቶ በተቀበረበት፤ በህወሃት (ወያኔና) በአሁኑ የኦህዴድ መደመር (መደበር) የዓብይ አህመድ አምባገነን አገዛዝ ዘመን፤ የፈጠራ ሥራውን በድፍረትቀረበ፤ ሰው በጠፋበት ዘመን፤ ሰው ሆኖ የተገኘ የጥበብ ሰው ነው ::

ጭው ባለው በረሃ፤ ድምፁን ከፍ አድርጎ፤

ሃገር መፍረሱን
የወገኖቹን መከራና ስቃይ
ረሃብና ችግር፤
መፈናቀልና ስደትን

ሳይደብቅ፤ ዕውነትን የሚናገር፤ ፍቅርን የሚሰብክ፤ ሃቀኛ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ !!  

እንደ መዝጊያ፤

የተፈጥሮ ህግ ሆኖ፤ ይመሻል ይነጋል፤ እያንዳንዱ ቀንና ሌሊት፤ የራሱ የሆነ ቅራንቅንቦ በማግተልተል፤ ተሸክሞ ይሁን አዝሎ፤ አንጠልጥሎ ይሁን ታቅፎ፤ እየሳበ ይሁን እየገፋ፤ ብቻ እንዳመቸውና እንደቻለው፤ እንደወደደውና እንደፈቀደው፤ ጓዙን ሸክፎ ወይምጠቅልሎ ይነጉዳል::          

አንዳንዴ በተቃራኒው፤ ለሰው ፍቃድና ይሁንታ ሳይገዛ፤ በፈጣሪ ይሁን ወይ በአንድ ባልታወቀ ሃይል ሳይገደድ፤ ሌሎች በቀደዱለት ቦይ ለመፍሰስ እምቢ ብሎ፤ እራሱ በፈጠረው ምህዋር ዙሪያ እየተሽከረከረ፤ የጊዜን የፍሰት ቀመር ከተለምዶ ሁነቱ ውጪ በመለካት ዜናን ያበስራል ::

አቆጣጠርና አለካኩ፤ ሰዓትን በሴኮንድና በደቂቃ፤ርቀትን በሜትርና በኪሎሜትር፤ ክብደትን፤ በግራምና በኪሎግራም፤ ዕድሜን ከወራትና ከዓመታት፤ አቆጣጠር ውጪ : የራሱ በሆነ ምህዋር ዙሪያ ያሽከረክራል ::

ታዲያ ያን ጊዜ : ሊነጋ ሲል መጨለሙን ያበስራል !!

ምርጫው በእጃችን ነው

ወይ በድንቁርናችን አብረን እንጠፋለን !!

ወይ በብልህነታችን አብረን እንኖራለን ::

ለራሳችን ስንል እንጣፍጥ !!

ቴዲ !

እኛ የአራዳ ልጆች በሙሉ፤

አብሽር !! አብሽር !! ብለናል

እንዳልከው ባንዲራውን ከፍ አድርገን የምናነሳበትን…ወ…ቀ…ሰ….ደ……. ::

ናንተው  ከድር ጠንክር  ከመርካቶ ::

ይችን መልክቴን ያነበባችሁ፤ እንዳለፈው ጊዜ : ለሌሎች ወገኖቻችን፤ በድረ ገጾቻችሁ፤ በዩ ትዩብ፤ በቲክቶክ፤ በፌዝቡክ፤ በፈረስ፤ በጋሪ በእግር እየሄዳሁ አድርሱልኝ ::     አደራ !!

ሥነ ጥበብን*1

ሙዚቃ፤ዘፈን፤ ግጥም፤ ሥዕል፤ ስነጽሁፍ (ልብ ወለድታሪካዊ)፤ ተውኔት ቲያትር፤ ጭፈራ፤ ዳንስ፤ ሽለላ፤ ፉከራ፤ ሙሾ …..ወዘተ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.