>
5:42 pm - Saturday March 20, 5909

ለዞን ዘጠኝ ጦማሪያን መታሰቢያ

  ሰውን አስሮ ይዞ ማስቀረት አይቻል
  በግዞት ቤት አስሮ ከሰውም ቢለያይ
  አካልን ነው እንጂ መች ሀሳብ ሊታሰር
  ሁሉን ይፅፈዋል በአዕምሮው ማህደር
 
  እናም ሰውን ማሰር አይደለም መገደብ
  ካሰበው እንዳይደርስ አይቻልም ማቆም
  ቢሆንም መታሰር እንዲሆን አውቃለው
  መፈታት አይቀርም ቀን አለው ቀን አለው
 
 የሀገርን ችግር መፃፍ ወንጀል ሆኖ
 ሰዎች ይገባሉ በወህኒ ታጉሮ
 እናም ወንጀላቸው ሲጠየቅ በይፋ
 ህገ መንግስት መናድ! አረ ፍትህ ጠፋ
 
  ምንም አይነት ወንጀል ሳይኖር ለአመታት
  ታስረው ይከርማሉ በጨለማ ግዞት
  መገረፉ አይጣል ኤሌትሪኩም አለ
 ባልሰሩት ወንጀል ላይ እመኑ እያለ
 
  ማመን መች ነው ቀላል ሞት እኮ ይሻላል
  ባልሰሩት ወንጀል ላይ ቲያትር ቀላቅሎ
  በእመን አትመን በዱላ አባሮ
  ይቅርታ ጠይቁ ይላል ውሎ አድሮ
 
  ስጋ እንኳን ቢቃጠል ለእውነት ቢከፈል
  አጥንትን አውጥቶ ህመሙ ቢያይል
  እውነት ነው ሚያሸንፍ የማታ የማታ
  ሀሰት ይወድቅና እውነት ነፃ ወጥታ
 
    ዘ-ፀአት ዞን ፱ ጦማሪያን ባሰብኩ ጊዜ
     ኒኮልሰን እስትሪት
    ገጣሚ-ሚካኤል ካሳሁን
Filed in: Amharic