የኢህአዴግ መንግስት ላለፉት 10ና 15 አመታት የአፈፃፀም ግምገማ ባደረገ ቁጥር ወይም እንደ ባለፈው አመት አጣዳፊ የሆነ ፖለቲካዊ ቀውስ ባጋጠመው ቁጥር “ለመንግስታዊ ስርዓቱ አደጋ” በሚል የሚጠቅሳቸው ሶስት ችግሮች በዋናነት በሶስቱ አባል ድርጅቶች ያነጣጠሩ ናቸው፡፡
1ኛ) “ትምክህተኛ” ማለት “ለሁሉም ነገር እኔ አውቃለሁ” የሚል ሲሆን በኢትዮጲያ ፖለቲካ ውስጥ ከሕወሃት በላይ ትምክህተኛ ቡድን ፈልጎ ማግኘት ይከብዳል፡፡ ለምሳሌ፣ የሕወሃት የሰሞኑ አጀንዳ ብአዴንን ከኢህአዴግ ውስጥ አስወጥቶ፥ ሱማሌንና ቤኒሻንጉልን አስገብቶ፣ ደህዴንን ለሁለት ሰንጥቆ፣ … እየተባለ ይዶለታል፡፡ ከዚህ በላይ “እኔ አውቃለሁ” የሚል የትምክህተኛ አመለካከት ብአዴን ሆነ ኦህዴድ ውስጥ ከቶ አይገኝም፡፡
2ኛ) “ጠባብ ብሔርተኛ” የሚለው ቃል “ፍቺ ስለ ራስ ብሔር ብቻ ማሰብና ማዳላት፣ ለሌሎች ጥላቻ ማሳየት” የሚል ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ ከሕወሃት የበለጠ ማሳያ መጥቀስ ይከብዳል፡፡ ከፓርቲው አመሰራረት እስከ ፌደራሊዝም ስርዓት በግልፅ የሚስተዋለው የሕወሃት ጠባብ ብሔርተኝነት ነው፡፡ ሕወሃት ሰራሹ ኦህዴድ ቀርቶ
3ኛ) ስለ ሕወሃት “ኪራይ_ሰብሳቢነት” ብዙም ማለት አያስፈልግም፡፡ “Rent Seeking” ማለት ያልተገባ ጥቅም መፈለግ ነው፡፡ ያልተገባ ጥቅም ማለት፣ ለምሳሌ
በአጠቃላይ፣
ስለዚህ፣ የኢህአዴግ መንግስት ላለፉት 10ና 15 አመታት “ለመንግስታዊ ስርዓቱ አደጋ” በሚል የሚጠቅሰው ‘ትጠብ-ኪስ’ ነው፡፡ “ትጠብ_ኪስ” ማለት ሕወሃት፣ “ሕወሃት” ትጠብ_ኪስ ነው!! ስለዚህ፣ ኢህአዴግ እንደ ፓርቲ ሕልውናውን ለማስቀጠል የትጠብ_ኪስን ችግር ከውስጡ ማስወገድ አለበት! ኢህአዴግ ሕልውናውን ለማስቀጠል ሕወሃትን ከውስጡ ማስወገድ አለበት፡፡