በአንድ በኩል ምርጫውን በማራዘም እስከ ቀጣዩ ጉባኤ ህወሓት በም/ሊቀመንበሩ ዶ/ር እየተመራ ለማስቀጠል፣ በሌላ በኩል ደግሞ ወ/ሮ ፈትለወርቅን () የድርጅቱ ሊቀመንበር አድርጎ ለመሾም ሲደረግ የነበረው የህወሓት ጨዋታ ተጠናቋል፡፡ በመጀመሪያው ግማሽ ጎል ያስቆጠረው በሁለተኛው አጋማሽ ባደረገው የመከላከል ጨዋታ ሞንጆሪኖን ከዋና ሊቀመንበርነት ወደ ምክትል ሊቀመንበርነት በማውረድ ነጥብ ጥሏል፡፡ በሁለተኛ አጋማሽ አጥቅቶ ሲጫወት የነበረው ደግሞ ሞንጆሪኖን ጠልፎ በመጣል ደብረፂዮንን ወደ ዋና ሊቀመንበርነት እንዲመጣ አድርጏል፡፡ በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ ከተጫዋቾች ጥፋት ተሰርቶብኛል በሚል ጨዋታውን አቋርጣ በመውጣቷ ምክንያት ከጨዋታ የታገደችው በቀጣይ ቅጣቱ ሊነሳላት እንደሚችል ይገመታል፡፡
በጨዋታው ሁለተኛ አጋማሽ ከራዕይ ቡድን ደጋፊዎች ሲሰማ ከነበረው የድጋፍና ተቃውሞ መፈክር ውስጥ፣ << አጥንት ይወጋናል>> የሚል ይገኝበታል፡፡ በተለይ ደግሞ በውጪ የሚኖሩ የራዕይ ደጋፊዎች <<እናከብራችኋለን እንጂ አንፈራችሁም!>> የሚል መልዕክት በስልክና ኢሜል አድራሻዎች በገፍ ሲልኩ እንደነበር ታውቋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ፣ የህወሓት የቢዝነስ ኢምፓየር ቤተሰብ ተጠቀለለና “ከEFFORT ያለ አግባብ የወሰድከውን 30 ሚሊዮን ዶላር መልስ” እና “ባለቤት የሌለው መስሎኝ ነው የወሰድኩት” በማለት ሲነታረኩ እንደነበር ውስጥ አዋቂያችን ከስፍራው ዘግቧል፡፡
በዚህ መሠረት፣ ሁለቱም ቡድኖች በሁለት ጨዋታ ተሸንፈው አንድ አቻ ወጥተው በአንድ-አንድ ነጥብ ወደ ቀጣዮ ዙር ሳያልፉ ቀርተዋል፡፡ ከምድቡ 2 ጨዋታ አሸንፎ፣ በአንዱ አቻ የወጣው 7 ነጥብ አንደኛነት ወደ ቀጣዩ ዙር አልፏል፡፡ ወጥ አቋም ማሣየት የተሳነው ፤ በመጀመሪያው ጨዋታ አሸንፎ፣ በሁለተኛው ደግሞ ተሸንፎና በመጨረሻው ዙር ጨዋታ አቻ ወጥቶ በ4 ነጥብ ወደ ቀጣዩ ዙር በሁለተኝት አልፏል፡፡ ሌላኛው ተወዳዳሪ በከፍተኛ ግራ መጋባት ውስጥ በመሆኑ ምክንያት ራሱን ከውድድሩ ማግለሉ ይታወሳል
