የኦህዲድ መሪዎች በኢህአዲግ ግምገማ እና ስብሰባ ላለፉት 18 ቀናት ያደረጉትን አኩሪ ታሪክ በፊት ለፊት ብያደርጉ መላው የኢትዮጵይም ህዝብ ከጫፍ ጫፍ ከአይን ያውጣችሁ ብሎ እንደሚያጨበጭብላቸው ምንም ጥርጥር የለኝም። አሁን ግን ነገሮች በፍጥነት እየተለዋወጡ ነው። አሁን ግን ህዝቡ አይናችሁ ይውጣ ማለት ጀምሯል።እሄ ደግሞ ምክንያቱ ኦህዲድ ገና የረጋ ደጋፍ አለፈራም።ደጋፍዎቹ በኦህዲድ የ27 ዓመት አስቸጋር ጉዞ ውስጥ አልፈው የመጡ ስለሆነ ኦህዲድ የሚሰራቸው መጠነኛ ስህተቶች እንድንሸራተቱ ያደርጋቸዋል።
ስለዚህ ኦህዲድ በሆነ መልኩ ስለ ሰሞኑ ስብሰባ በመጠኑ እንኳን ነገሮችን ግልፅ ካላደረገ በስተቀር በቋፍ ላይ ያለው የኦሮሚያ ሁኔታ መተረማመሱ ነው። ከተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች የሚመጡት መረጃዎች እንደሚያሳዩት በወጣቱ መሃል ከመግለጫው በኃላ ተክደናል የሚል ወሬ እንደሰደድ እሳት እየተሰራጨ ነው።
ስለዚህ የኦህዲድ ስራ አስፈፃሚን ቀላል ነገር እንዲያደርግ ብቻ እንጠይቃለን። ሌላ ስራ ስራ እያልናችሁ አይደለም። በቃ የሚያስመሰግናችሁን ነገር አርጋችኃላ።እሱን በመጠኑ ለህዝብ ግለፁ። ያለምግባራችሁ በቋፍ ላይ ያለውን ኦሮሚያ እሳት ውስጥ አትክተቱ። ኢህአዲግንም ሆነ ሀገሪቷንም እንድትፈርስ ምክንያት አትሁኑ።
ይህ ነገር በፍጥነት ካልሆነ ከተወሰነ ጊዜ በኃላ ጥቅም የለውም። መፍጠን ያዋጣል።