>

ምንድን ነን ግን? (አቻምየለህ ታምሩ)

ከአራት  አመታት በፊት ዶክተር በድሉ ዋቅጅራ ትውልዱን በሚመለከት አንድ ገላጭ ንግግር አድርጎ ነበር። ንግግሩ. . . 

«ትውልዱ ለትልልቅ ነገር አይኑ ተጨፍኗል። ይህ ትውልድ ሁለት አይኑን አጥፍተህ ነጭ ዱላ ብታስጨብጠው ስላጠፋኸው አይኑ አያማርርህም፤ ስለፈቀድክለት በትር ግን ሊያመሰግንህ አደባባይ ይወጣል» የሚል ነበር። ይህ  የዶክተር በድሉ ዋቅጅራ ንግግር  ዛሬ ወያኔ ጊዜ ለመግዛት  ሲል  እየተጫወተ ያለውን ቁማር የሚያመሰግኑትን   ምስኪኖር የሚገልጽ ይመስለኛል።  ለዚህም ነው የጽሁፌን ርዕስ ምንድን ነን ግን? ስል የሰየምሁት።

ሶስት ትውልድ ንጹሀንን በግፍ  አስሮ  ገላቸውን ሲተለትል፤ ጸጉራጨውን  በደረቁ ሲነቅል፤ ጺማቸውን ሲነጭ፤ የእግርና የእጅ ጥፍሮቻቸውን  በጉጠት ሲያወልቅ፤ በብልታቸው ላይ የታሸገ ውሃ እንዲንጠለጠል በማደርግ ሲያኮላሽ፤ በኤሌክትሪክ ሽቦ ሰውነታቸውን   ተልትሎ  ሲያቃጥል፤  እንደ ክርስቶስ  በመስቀል ላይ ሰቅሎና  ዘቅዝቆ በማሰር   በግፍ ሲደበድብ የኖረውን የምድራችን ጨካኝ አገዛዝ፤  እንቅልፍ እንዳያገኙ፣ ለብቻቸው እንዲታሰሩ፣ ውሃ ውስጥ እንዲዘፈቁ፣ ተገደው የራሳቸው ያልሆነውን ቃል የራሳቸው እንደሆነ አድርገው በማስፈረም በግፍ ሲያስር የኖረ፤ አንዱ እስረኛ ሌላውን እንዲደበድብ  ሲያደርግ የባጀን፣ በማሰቃየት  እልቆ ቢስ የህሊና ታሳሪዎችን የገደለ፤ በታሰሩበት በእሳት የማገደና  በማንነታቸው  ሲዘልፍ፣ ሲያዋርድና የስነልቦና ጉዳት ሲያደርስ  ዘመኑን በሙሉ የኖረ የፋሽስት አገዛዝ በሕዝባዊ ተጋድሎ  ግማሽ ህይወቱ ወደ ሞት ተለውጦ እውር ድንብሩን እየሄደ ከሚገኝበት የፍጻሜው አጋማሽ ላይ ደርሶ አንድም የፖለቲካ እስረኛ የለም እያለ ሲያላግጥ እንዳልኖረ  ሁሉ  ጊዜ ለመግዛት  ሲል  «የፖለቲካ እሥረኞች ይፈታሉ» ስላለ ምስጋና ሲጎርፍለት አየሁ ልበል? እኛ ግን ምንድን ነን ጎበዝ?

በእርግጠኛነት መናገር እችላለሁ በወንጀል ክብረ ወሰን የተቀዳጀ አገዛዝ  በግፍ አስሮ ሲያሰቃያቸው የኖራቸውን የሕሊና ሰዎች ጊዜ ለመግዛት ሲል  ከጠባብ እስር ወደሰፊው እስር ቤት እንዲዘዋወር በረጅሙ አስሬ እለቃቸዋለሁ  ስላለ  እንደ በጎነት  ተቆጥሮለት  በምድር  ላይ  ሲመሰገን ያየነው  ብቸኛው  የአለማችን አፓርታይድ አገዛዝ ወያኔ ብቻ  ይመስለኛል!

ምድሪቷን በጭካኔ ያጨቀያት  የትግራይ አፓርታይድ አገዛዝ ሳይወገድና ሕዝባዊ መንግሥት ሳይቋቋም  ዛሬ የፖለቲካ እሥረኞች  ቢፈቱ ነገ ተመልሰው ወደ ዘብጥያ ላለመውረዳቸው ምን ዋስትና ኖሮ ነው ገና «የፖለቲካ እሥረኞች ይፈታሉ»  ስለተባለ ጮቤ የምንረግጠው? ከዚህ በፊትም ጨካኙ መለስ ዜናዊ «የአገር ሽማግሌዎች» የሚባሉት እነ ፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሃቅ  የኢትዮጵያ ሚሊኒዬም በሚከበርበት ወቅት  «እስር ቤቱን  ሁሉ ባዶ አደርግላችኋለሁ» ብሎናል  ብለውን  ነበር። በተግባር ግን ከኢትዮጵያ ሚሊኒዬም በኋላ  ዘብጥያ የወረደውን  የህሊና እስረኛ  ብንቆጥረው በታሪካችን እስር ቤት ከገባው ቁጥር አንጻር  መለስ  ዜናዊ «እስር ቤቱን  ሁሉ ባዶ አደርግላችኋለሁ»  ካለ በኋላ  የታሰረው  በብዙ እጥፍ ይበልጣል።

በጣም አስቂኙ ነገር ደግሞ ማዕከላዊ ተዘግቶ ሙዚየም ይሰራበታል መባሉ ነው። ይታያችሁ! በማዕከላዊ የማሰቃያ ቦታ ላይ   ሙዚየም  እገነባለሁ የሚለን  ሲያሰቃዬን የኖረው የስቃዩ ጌታ ወያኔ ነው። አንድ እውነት አለ፤ በማዕከላዊ የማሰቃያ ማዕከል ሙዚየም መገንባት አለበት።  ሆኖም ግን ሙዚየሙ  መገንባት ያለበት ሲያሰያቃን በኖረው በግፈኛው  ክብረ ወሰን በሰበረው በወያኔ ሳይሆን በግፉዓን ታሳሪዎችና   ከወያኔ ግፍ በተረፉ ንጹሀን ኢትዮጵያውያን ነው።  ሲያሰቃየን የኖረው ወያኔ ማዕከላዊ ማሳቀያ ላይ ግርፋት ያብቃ ብሎ  ሙዚየም  ቢገነባ   እንደ ቀይ ሽብሩ የመታሰቢያ ሙዚዬም    a mockery of justice and history  የሚሆን  መሳቂያ የድንጋይ ክምር  ካልሆነ በስተቀር የግፍ ማድረቂያ  ቃል ኪዳን ሊሆን አይችልም። ወያኔ  በማዕካዊ ማሰቃያ ሲተለትለን የኖረው  የቀይ ሽብር የመታሰቢያ ሙዚዬምን  አዲስ አበባ  መሃል ላይ አቁሞ መሆኑን መዘንጋት የለብንም።

ባጭሩ  ኢትዮጵያ ውስጥ የታሰሩት  በግፍ  የእግር ብረት ውስጥ ሆነው  በትግራይ መርመሪዎች የሚሰቃዩት  የህሊና ሰዎች  ብቻ አይደሉም። ሁላችንም  ኢትዮጵያውያን  ከትግራይ በበቀሉ ፋሽስቶች  የማሰቃያ  እስር ቤት ውስጥ ነን።  ኢትዮጵያ ከፋሽስት ወያኔ የትግራይ የአፓርታይድ አገዛዝ እስር ነጻ ሳትወጣ «አሸባሪ» ብለው  በግፍ ያሰሯቸውን የህሊና ሰዎችን   በጭካኔ ካሰሩበት  ከጠባቡ የሰው መታረጃ ቄራ  ወደሰፊው የማሰቃያ  እስር ቤት  እንዲዘዋወሩ  በረጅሙ አስረው ስለለቀቋቸው ፍትህ የተገኘ፣ ሰላም የመጣ፣ ነጻነት የተጎናጸፍን አድርገን አንቁጠረው።  በቃላት ከሚገለጸው በላይ ጨካኝ ወንጀለኛ የሆነው ወያኔ ከነ ሕገ አራዊቱና የአፓርታይድ ድንጋጌው  ተወግዶ ግፈኞች እኛን ያሰቃዩበት እጃቸው የኋሊት  በመጫኛ ታስሮ  እውነተኛ ችሎት  ፊት  ቀርበው ለፈጸሙት ጭካኔ  ፍርዳቸውን እስካላገኙ ድረስ ለትንፋሽ ማግኛና ለጊዜ ለመግዣ ብለው «የፖለቲካ እሥረኞች ይፈታሉ» ስላታለሉን በወያኔ ግፍ በጨቀየችዋ ኢትዮጵያ ስርየት ሊኖር አይችልም።

ኦሮማራ  ይለመልማል!  ሕዝባዊ ትግሉ ተጠናክሮ  ይቀጥላል!

Filed in: Amharic