መግለጫው አሁን ያለውን የኢኮኖሚ ቀውስ ይበልጥ የሚያባብሰው ይሆናል። ባለሃብቶች ሃብታቸውን ለማሸሽ ባንኮችን ማጨናነቃቸው አይቀርም። ብሄራዊ ባንክ ከባንክ የሚወጣውን የገንዘብ መጠን የሚወስን ህግ ሊያወጣ ይችላል። ባንክ ቤት ውስጥ ገንዘብ ያስቀመጡ ሰዎች ገንዘባቸውን አውጥተው ፍራሽ ስር ቢደብቁት ተመራጭ ይሆናል። እገዳ ከተጣለ በሁዋላ ገንዘብ እንደ ልብ ማውጣት ላይኖር ይችላል። ዲያስፖራውም ዶላር ልኮ ቅጠል ታቅፎ እንደሚቀር በመገንዘብ፣ ዶላር ከመላክ ቢቆጠብ ካልታሰበ ኪሳራ ይድናል። የመሬትና የቤት ዋጋም ይወድቃል። በተለይ ኪራይ ለመብላት ሲሉ በባንክ ብድር ህንጻዎችን የሰሩ ሰዎች፣ ከፊታቸው ትልቅ ፈተና ይጠብቃቸዋል።
ህወሃት ከተወሰኑ ዓመታት በፊት የገንዘብ ግሽበት እና የዶላር እጥረት በአፍጢሙ ሊደፋው ሲቃረብ 20/80 ….40/60… ምናምን …የሚባሉ ማጭበርበሪያዎች አምጥቶ ትንሽ ተንገዳገደ ፡ አሁን የፖለቲካውም ቀውስ ተደርቦበት የመውጪያ መንገዱን ማሰቢያም ግዜ የላቸውም አሁን ሁሉም ለፍርጠጣ አቆብቁቦ ነው ያለው ከአገር ቤት እንደሚሰማው ብር ወደ ዶላር የመለወጥ ሩጫው ተጧጡፏል ለኢትዮጵያ ገንዘብ ያበደሩ አገሮች ሁሉ “ገንዘባችን” የሚሉበት ወቅት ላይ ነን፤ ለእነሱ የሚከፈለው ገንዘብ ከየት እንደሚመጣ የሚያውቀው፣ አንድዬ ብቻ ነው። ድሮ ከየትም ቀፍሎ ዶላር የሚያመጣውና የወያኔን ጓዳ ሸፍኖ የጭንቁን ጊዜ የሚያሳልፈው አላሙዲን ዛሬ የለም። ወያኔ በዚህ ሁሉ መሃል፣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማውጣት በራሱ ላይ የሞት አዋጅ አውጇል።
በተያያዘ- የትግሉ አላማ ፣ በህዝባዊ ምርጫ፣ አንዱን ስርዓት በሌላ ስርዓት ለመተካት ነው