>

ጣይቱ የባሕልና የትምህርት ማዕከል 19 ነኛ ዓመት አብራችሁት እንድታከብሩ ይጋብዛል

ጣይቱ የባሕልና የትምህርት ማዕከል ባለፉት 19 ዓመታት በስደት ዓለም ሊከናወኑ ሳይሆን ሊታሰቡ የሚከብዱ በርካታ የጥበብ ሥራዎችን በሚያኮራ ውጤት አከናውኖአል:: በጥቂት ቀና ሰዎች ድጋፍ ባለማቋረጥ ጥበብን በጥራት በመላው ሰሜን አሜሪካ በካናዳና በአውሮፖ እየተዘዋወረ ከሃገሩ ውጭ የሚገኘውን ኢትዮዽያዊ ሲያዝናና ሲያስተምር ቆይቷል:: የኢትዮዽያን ታሪክና ባሕልና ጥበብ ሲያቀርብ እነሆ 19 ዓመታትን አስቆጠረ:: ያልተቋረጠ 230 የግጥም ምሽቶችን አስተናግዷል:: ከአንጋፋዎቹና ዕውቆቹ ፀሐፊያን ከነሎሬት ፀጋዬ ገ/ መድህን- ከሰለሞን ደሬሣ – ከሰይፉ መታፈሪያ- ከማሞ ውድነህ- ከተስፋዬ ገሠሠ- ከዶር ፈቃደ አዘዘ – ከፕሮ አዱኛው ወርቁ . . . ጀምሮ በሕይወት እያቀረበ ሥራቸውን ዘክሮአል::

ወጣት ፀሐፊያንን በማበረታታት ፅሑፋቸው ለሕትመት እንዲበቃ በማድረግ አስመርቋል:: በአጠቃላይ 3555 የግጥም አንባብያንን አስደምጧል:: ከ50 በላይ ዕውቅ ተዋንያን በድርጅቱ ምርጥ ተውኔቶች የተሳተፉ ሲሆን በሄደበት አካባቢ ሁሉ ሙያዊ ሥልጠና በመስጠት 103 አማተር ተዋንያንን በመድረክ አሳትፏል:: 271 የቴአትር ጉዞዎችን ያደረገ ሲሆን 378 ትርኢቶችን ለተመልካች አቅርቧል:: በየዓመቱ ህዳር ወር ነፃ የሙያ ሥልጠና በትወና – በፅሑፍ -በዝግጅት- በሲንማ ጥበብ በጋዜጠኝነት ወዘተ ከመስጠቱም ባሻገር በዕውቅ የዩኒቨርሲቲ ምሁራን በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ዘውትር አርብና ቅዳሜ ነፃ Tutering በመስጠት ወጣቶችን ይረዳል :: የመጀመሪያውን የአማርኛ ቤተመፃህፍ ከፍቶ የአማርኛ መፃሕፍትን ለሚፈልጉ አገልግሎትይሰጣል:: በአሁኑ ጊዜ ጣይቱ ማዕከል ከኢትዮጵያውያን አልፎ የአፍሪካውያን መሰባሰቢያና ኩራት ነው::

እጅግ የሚያኮራና የሚያስደንቅ ክንውኖችን ያስመዘገበው ድርጅት 19 ነኛ ዓመቱን September 22nd, 6:30 at Civic Building, Silver Spring MD አብራችሁት እንድታከብሩ ይጋብዛል::

Filed in: Amharic