>

እውነት እውነት እላችኋለሁ፤ ኦሮሙማ ከአሁን በኋላ አንድ ዓመት ሥልጣን ላይ ከቆዬ …. (ይነጋል በላቸው)

እውነት እውነት እላችኋለሁ፤ ኦሮሙማ ከአሁን በኋላ አንድ ዓመት ሥልጣን ላይ ከቆዬ ….

ይነጋል በላቸው

ወቅቱ የተግባር እንጂ የንግግር አለመሆኑ ይገባኛል፡፡ ለንግግሩም ቢሆን ከሁለትና ሦስት አሠርት ዓመታት በላይ ስለጮህንና ጮኸታችንም በእግዚአብሔር ዘንድ ዋጋ ተሰጥቶት የመጨረሻው የትንሣኤያችን ምዕራፍ ላይ ስለደረስን የቀደመ ጩኸታችንን ዋጋ አናሳጣውም፡፡ ለማንኛውም በሰሞነኛው የሀገራችን ሁኔታ በቴሌግራም ገፆች ከተመላለስንባቸው ሃሳቦች መካከል የተወሰኑትን እዚህ ላይ ማቅረቡ ክፋት የለውምና የፈለገ ያዝግምበት፡፡ ፋኖ ግን ጠቃሚ ሃሳቦችን ስለሚያገኝበት በዚያ ሠፈር የምትገኙ ጓዶች ይህን መልእክት እንድታደርሱ ትለመናላችሁ፡፡ የሃሳብ ትንሽ የለውም፡፡

ትናንት ማታ ከሰጠሁት አስተያየት ልጀምር፤

አንዳንድ ነጥቦች ለፋኖ ሠራዊት፡-

– በተለይ ኦሮምኛና ትግርኛ የሚችሉ የፋኖ  አባላት ምርኮኞችን በማንቃት ረገድ ትልቅ ሚና አላቸውና ይታሰብበት፡፡ እውነተኛውን የአማራ ትግል ዓላማና ግብ ለተወናበዱት የሌላ ብሔር አባላት ይበልጥ ለማስረዳት የራሳቸውን ቋንቋ መጠቀም ተገቢነት አለው፡፡ የተጣመመን ለማስተካከል የቋንቋ ዕውቀት ወሳኝ ነው፡፡ አንድ ሰው ደግሞ በቋንቋው ሲያስረዱት በደምብ ይገባዋል፡፡ ቋንቋ ደግሞ የመግባቢያ መሣሪያ እንጂ ኦነግንና ወያኔን መሰል ጠባቦች እንደሚያወሩት የግል ንብረትና ከዘር የሚወረስም አይደለም፡፡ አንድ ቋንቋ ከአንድ ሹካ ወይንም ማንኪያ የበለጠ አገልግሎትም ሆነ ፋይዳ የለውም፡፡

– ስሜትን ከሚያጎፈንን ወይም ልዩነትን ከሚያሰፋ ንግግርና የቃላት አጠቃቀም  እንዲሁም የሰውነት ቋንቋ መቆጠብ አስፈላጊ ነው፤ ለትግሉም አሉታዊ እንጂ አወንታዊ አስተዋፅዖ የለውም፡፡ ለምሣሌ ኦሮሞ መባልን ለሚፈልግ ሰው – ምንም እንኳን ቃሉ በራሱ ክፋት አለው ብዬ ባላስብም – “ጋላ” ብሎ መጥራት ትክክል አይደለምና ይታረም፡፡ የአማራ ሆደ ሰፊነትና ከሁሉም ጋር ተግባብቶ የመኖሩን ባህልና ወግ ልማድ ከሚያጠለሹ መጥፎ ልማዶች መቆጠብ ተገቢ ነው፡፡ ሞኝና ሞኝ ነገር ሲያከር ነገር ይበላሻል፡፡

– የሚማረኩ መኪኖችንና ሌሎች ንብረቶችን አለማቃጠል፡፡ ቢቻል በነሱ መገልገል፡፡ ያ ባይቻልና ጠላት ሊጠቀምባቸው ይችላል ተብሎ ከታመነ መደበቅ ወይም እንዳይሠሩ በባለሙያ አንዳንድ ዕቃዎችን ፈትቶ በሥውር ቦታዎች ማስቀመጥና በድል ማግሥት ገጣጥሞ መጠቀም፡፡ ንብረትን ለማውደም በሚያስችል ደልቃቃ የኢኮኖሚ ደረጃ ላይ ስለማንገኝ ከእልህ ይልቅ ብልኅነትና ጥበብ እንደሚጠቅመን እንረዳ፡፡

– ዘመነ ካሤን የመሠሉ የከተማ ውስጥ ፋኖዎችንና አስመሣይ ብአዴኖችን መጠንቀቅ፤ ለነሱ ምሥጢር አለማካፈል፤ አመኔታን መገደብ፤ ሰው መሣይ በሸንጎዎችን መለየትና በተገቢው መንገድ መያዝ …

– ለሽምግልና የሚመጡ ቄሶችንና ሼሆችን እግር እግራቸውን ቀንድቦ ደሮ ጠባቂ ማድረግ፡፡ የአማራ ፋኖ ትግል ኦሮሙማን እስከወዲያኛው ቀብሮ አራት ኪሎን ካልተቆጣጠረ አማራ ብቻ ሣይሆን መላዋ ኢትዮጵያ በተጀመረው ኦነጋዊ የጥፋት ጉዞ ጨርሳ እንደምትወድም መገንዘብና ለትልቁ ዒላማ መትጋት፡፡

– የተጀመረውን ትግል ግለቱ ሳይበርድ ከአማራ ክልል በአፋጣኝ በማውጣት አማራ በጅምላ ወደሚታረድባቸውና በግሬደር ወደሚቀበርባቸው አካባቢዎች ዘልቆ በመግባት ቆንዳላ ወሴዎችን የጃቸውን በመስጠት የምስኪን ወገኖችን ዕንባ ማበስ ይገባል፡፡ ከዚህና ከመሳሰለው የመፍትሔ እርምጃ ውጪ ያለው ሁሉ እርባናቢስና የጠላትን ጭካኔ ይበልጥ የሚያከፋ ሸምቀቆንም የሚያጠብቅ መሆኑን መረዳት፡፡

– የአማራ ዋና ጠላት ከወያኔና ልጁ ኦህዲድ ይልቅ በውስጡ እሱን መስሎና የሱን ቋንቋ እየተናገረ በስሙ የሚነግደው በብአዴንና በመከላከያው የመሸገው ሆዳሙ አማራ መሆኑን በመረዳት ከለየለት የአማራ ጠላት አስቀድሞ በተጠና መልኩ ይህን የይሁዳ ሽንት ማድረቅና የጠላትን ቅስም መስበር፡፡ ለዚህ ደግሞ የእናት ልጅም ቢሆን በፍጹም አለመራራት፡፡ አማራ ከምድረ ገጽ እንዳይጠፋ ከተፈለገ ለምሣሌ የኦህዲዱ ኮንዶም ኮ/ል ጌትነት አዳነ  በተቻለ ፍጥነት መወገድ አለበት – አጉል ይሉኝታ ያጠፋል፡፡ ወደፍርሀት የተጠጋ አጉል ርህራሄና ገደቡን ያለፈ ትግሥት ባለፉት 50 ዓመታት አማራን ምን ያህል ከባድ የኅልውና ኪሣራ ውስጥ እንደዘፈቀው እናውቃለን፡፡ ይሄ ሀብትና ሥልጣን – ሊያውም በቅጡ የማይሠራበት ፍርፋሪ ሥልጣን – ሥንቶችን እንዳማለለና በዚያም ሳቢያ ለገዛ ወገናቸው መጨፍጨፍ ዋነኛ ምክንያት እንደሆነ መረዳት አይከብድም፡፡ የእናት ሆድ ዥንጉርጉር መሆኑ የሚነገረውም ለዚህ ነው፡፡

– ነፃ የሚወጡ ከተሞችና አካባቢዎች ጠንካራ ሰዎች ይመደቡባቸው፡፡ ፍትሃዊ አስተዳደር ከወዲሁ ይታይ፡፡ ለሕዝብ ድጋፍ ቀጣይነት መሠረቱ ይሄው ነውና ይህ ነገር ትኩረት ይሰጠው፤ በተጀመረው መልክ ይቀጥል፡፡ ድሉ አድማሱን እያሰፋ ሲመጣ የተደበቁ መልካም ሰዎች ይወጣሉ፤ የየሙያቸውን አበርክቶም ይሰጣሉ፡፡ ጨካኝና ዐረመኔ ሰይጣን ነግሦብን እንጂ ሀገራችን የወላድ መካን እንዳልሆነች ሰሞነኛው የአማራ ፋኖ ግሥጋሴ ዋቢ ነው፡፡ እንደሚታየው ሤራና የሆዳሞች አሻጥር ቢሆን ኖሮ ይሄኔ አቢይ መቄትና ላሊበላ ላይ ባሽቃነጠብን ነበር፡፡ ይህን ሃሣቤን ለፋኖ በአፋጣኝ አድርሱልኝ ታዲያ፡፡

– በደስታም ሆነ በሀዘን ጥይትን ማባከን ይቁም፡፡ አማራ መተኮስ ይወዳል፡፡ ግን አሁን ባለብን የመሣሪያ ውድነትና ዕጥረት እንደጥንቱ መጓዝ አይቻልምና በልቅሶም ሆነ በሠርግና በድግስ ወደሰማይ በከንቱ የሚረጨው ጥይት ይቁም፡፡ 

– በመምህር ዘመድኩን የተነገረውና በቅጽበት ወደተግባር እየተሸጋገረ ያለው በአማራ አካባቢ ወኔ ሰላቢ የሆኑ የቁማርና የጫት የመጠጥና የሀሽሽ ቤቶችን በአፋጣኝ መዝጋት፡፡ እዬዬም ሲደላ ነው፡፡ ያ ዓይነቱ ማኅበራዊ ነቀርሣ አስፈላጊ ከሆነ እንኳ ሀገር ሲኖረን ይደርሳል፡፡ በግሬደር እየተቀበርንና ከያለንበት እየታረድን እንዲህ መቅበጥ ለጠላት ምቹ መሆን ነውና ይህ ነገር ዘመቻ ይደረግበት፡፡

አንድ ሰው ከፍ ሲል የተቀመጠውን አስተያየቴን አንብቦ ስለዘመነ ካሤ በተናርኩት ላይ ቅሬታ አዘል ጥያቄ ጠየቀኝና የሚከተለውን መልስ ሰጠሁ፡-

ግሩም ጥያቄ ነው፡፡ ሃቀኛ ፋኖዎች በረሃ ለበረሃ እየተንከራተቱና ባሉበት የኦሮሙማ ጦር ዘምቶ እየተዋጋቸው ሣለ ዘመነ ባሕር ዳር ውስጥ ተንቀባሮ የተቀመጠው የብአዴን ጃዋር ሆኖ ወይንስ አንዳች ምትሃት አለው? ለዚች ሚጢጢ ጥያቄ ብቻ መልስ ሰጠኝ፤ ሌላውን ጊዜ ይመልሰዋል ከተሳሳትኩም ተንበርክኬ ይቅርታ ለመጠየቅ ዝግጁ ነኝ፡፡ But many things of him seem to be highly fishy, in case we get along with this second language of all of us.

ልብ አድርግ ወገኔ!!!

ዛሬ ወደ ንግድ ባንክ ጎራ አልኩ፡፡ ባልተለመደ ሁኔታ በየመስኮቱ ሁለት ሁለት ሠራተኛ አለ፡፡ አገልግሎቱን የሚሰጠው ተለማማጅ ሲሆን አለማማጁ ከጎኑ ያለው ነው፡፡ ትዝብቴን ስቀጥል አንድ ነገር ታወሰኝ፡፡ እሱም ባንክንም ሆነ ሌላውን የመንግሥት መሥሪያ ቤት ሰባና ሰማንያ ከዚያም በላይ ፐርሰንቱን ኦሮሞ፣ ሠላሣና ሃያ ከዚያም በታች ፐርሰንቱን ደግሞ ሌሎች ብሔር/ብሔረሰቦችን ለማድረግ ኦሮሙማ አቅዶ ወደተግባር መግባቱ ነው፡፡ ያኔ ነው ከጎን የተቀመጡት ነባር የባንኩ ሠራተኞች ነገ ጧት የሚተኳቸውንና ሥራ አጥ የሚያደርጓቸውን ሰገጤ ባላገር ኦሮሞዎች እያሰለጠኑ መሆናቸው የገባኝ፡፡ ትራፊክ ፓሊሶችን የማግኘት አጋጣሚ አለኝና ስታዘባቸው ከአሥሩ ዘጠኙ ኦሮሞ ናቸው፡፡ ባጭሩ ኦሮሞ ሁሉንም ተቆጣጥሯል፡፡ ይሉኝታ ብሎ ነገር ደግሞ አልፈጠረባቸውም፡፡ አዲስ አበባ በሚገርም ሁኔታና በሚያስደነቅ ፍጥነት የኦሮሙማ አንጡራ ንብረት ሆናለች፡፡ ከፈለጉ በምትተነፍሰው አየር ግብር ሊያስከፍሉህ ይችላሉ፤ ከፈለጉ ከሚስትህ ወይንም ከባልሽ ለምታገኙት ተፈጥሯዊ የፆታ ልዩነት ለሚሰጥህ ደስታ ከፍተኛ ቀረጥ ሊጥሉብህና መክፈል ካልቻልክም ሊያፋቱህ ይችላሉ፡፡ አማራን ማሰርና መግደል ለነሱ ቀላል መዝናኛቸው ነው፡፡ ባጭሩ አማራ የኦነግ/ኦህዲድ መጫወቻ አሻጉሊት ሆኗል፡፡

የጌታየን አነጋገር ልዋስ፡፡ እውነት እውነት እላችኋለሁ ኦሮሙማ ከአሁን በኋላ አንዲት ዓመት የአገዛዝ ዕድሜ ካለው አዲስ አበባ ውስጥ እንዲኖር የሚፈቀድለት አማራ – ሊያውም የለየለት ባሪያ ሆኖ – ግፋ ቢል ከሃያና ሠላሣ ሽህ አይበልጥም፡፡ የአማራው መደኽየት ብቻ ሣይሆን ቆሞ መሄዱና ብሶቱን በሆዱ ችሎ በፈገግታ መሣቁ ራሱ ኦነግ ኦህዴዶችን ያበሳጫቸዋል፡፡ አለመለከፍ እኮ ነው፡፡ በሉ በሉ ፋኖን ተል ተሎ በልና ከነዚህ ከጭራቅ የባሱ ዐረመኔ ጉግማንጉጎች ገላግለን በሉልኝ፡፡

በነገራችን ላይ እኔን ብቻ ይሆን ይቺን ሰሞን ደስ ደስ እያለኝ የመጣው?

አዎ፣ ከልደትና እርሱን ተከትሎ ከሚመጣ ደስታና ፈንጠዝያ በፊት ኃይለኛና አስጨናቂ ምጥ አለ፡፡ በዚያ ምጥ መሀል የሕጻኑ ወይም የእናቱ አንዳንዴም የሁለቱም መጎዳትና ለኅልፈትም መዳረግ ያጋጥማል፡፡ እኛን ምሥኪኖቹንም ሀገራችንንም ከዚህ ዓይነቱ ሾተላይ ይጠብቀን፡፡

ለኔ ሲሉ ሕይወታቸውን ለመገበር ጫካ የሚገኙ ፋኖዎችን እግዚአብሔር ከጎናቸው ሆኖ ይራዳልኝ፤ መስዋዕትነት የከፈሉልኝን በአፀደ ገነት ያኑርልኝ፡፡ ከተነሣው ወጀብና የመከራ ዶፍ ለመትረፍ አብቅቶኝ የሆነ በጎ አድራት ድርጅት በስማቸው አቋቁሜ የሰማዕታቱን ቤተሰቦች በሚያስፈልጋቸው ሁሉ ለማገዝና በሞራል ለማበረታታት እንድችል ፈጣሪየ ዕድሉን አይንፈገኝ፡፡ አሜን ነው – ከአሜን ይቀራል፡፡

ዛሬ ሌሊት ላይ የሰጠሁት አንድ አስተያየት፡-

“ለዐማራ ፋኖ ስንቁን ገበሬው፣ ትጥቁን ከጁላ ሠራዊት፣ ወኔ ከራሱ፣ ድል ከእግዚአብሔር ይዞ ወደፊት ብቻ።” (በዘመዴ የቲጂ ፔጅ የሚታይ)

ፐ! ዘመዴ እኮ የልብ አድርስ ተናጋሪ ነው፡፡

ግን ግን “ቀበቶውን ቀርቶ ሱሪውን እናስወልቀዋለን” ባሉበት አንደበት ወስላታ ቄስና ሼካ ልኮ አስታርቁኝ ማለት አያሳፍርም? ለነገሩ ሀፍረት መች ያውቁና፡፡ ከአሁን በኋላ ማቄን ጨርቄን ማለት አያስፈልግም፡፡ ገጥመዋል ገጥመዋል፡፡ “ገጥመን መስሎኝ!” ብሏል ጎጄ ይሁን ጎንደሬ፡፡ እናሳ – ገጥመው መስሎኝ፡፡

ከአራት ኪሎ ያነሰ ድል አማራን ለማስፈጀት ካልሆነ አንዳችም ጥቅም እንደሌለው ለእውነተኛው ፋኖ በተደጋጋሚ ማሣሰብ ይገባል፡፡ ዘመዴ በተለይ ይህን ጉዳይ ለአፍታም እንዳትዘነጋ፡፡ ለነገሩ ትንቢቱም ስለደረሠ እነሱም ማለትም ፋኖዎቹም አያደርጉትም፡፡ እንደዚያ ቢያደርጉ በኢትዮጵያ ትንሣኤ ላይ በረዶ እንደማውረድ ነው፡፡ ሽምግልና የዕቃ ቃ ጨዋታ አይደለም፡፡ በአማራና በኦሮሙማ መካከል ያለው ቅራኔ ደግሞ በደም እንጂ በድርድር የሚፈታ አይደለም፡፡ ስለዚህ አሽቃባጩንና የትሮይ ፈረሱን ሁሉ በዋናነት ጨምሮ ሀገር አፍራሽን ሁሉ እነሱ በመጡበት መንገድ ገለል ማድረግ ይገባል፡፡ ከዚያ ሁሉም ይጠራል፡፡

አንድ ትልቅ እውነት ልናገር፡፡ መንጃ ፈቃድ ስናወጣ አንዳንድ የዋህነታችንን የሚፈታተኑ የጽሑፍ/የቃል ጥያቄዎች ይገጥሙናል፡፡ በሰብአዊነት ተታለን ጥያቄው ከሚፈልገው መልስ ዉጪ ከመለስን ፈተናውን እንወድቃለን፡፡

ለምሣሌ፤ “60 ሰው ጭነህ በፍጥነት ስታሽከረክር አንድ ሰው ቢገባብህ ምን ታደርጋለህ?” ተብለህ ልትጠየቅ ትችላለህ፡፡ ቀላል ጥያቄ ነው፤ መልሱም ቀላል ነው፡፡ አንዱን ገጭተህ ስልሣውን ማዳን፡፡

አማራንና ኢትዮጵያን ለማዳን ከተፈለገ በጣት የሚቆጠሩ ሆዳም አማሮችን በይሉኝታ ገመድ ታስሮ እሹሩሩ ማለት አይገባም፤ ብዙ ዋጋ ያስከፍላል – እያስከፈለንም ነው፡፡ ስለዚህ ዘመነ ካሤም ይሁን ዮሐንስ ቧ ያለው፣ እስክንድርም ይሁን መሣፍንት፣ ኮሎኔል ደመቀም ይሁን ምሬ ወዳጆ፣ አበጀ በለውም ይሁን ፊታውራሪ መሸሻ … ምን አለፋህ ማንም ይሁን ማን ከአማራ ኅልውና አይበልጥምና በአስተማማኝ መረጃና ማስረጃ ተደግፎ ነውሩ ከተጋለጠበት እቅጩን አሳውቆ ማስወገድ ወይም ከሰማ እንዲያርፍ መምከር ተገቢ ነው፡፡ በስመ ጥርነት ትግልን ማኮላሸት መቼም የማይስተካከል ችግር መፍጠር ነው፡፡ እኔም የማሸታቸው እንከኖች አሉ፡፡ ሁሉም ይገለጥ፡፡ የሚሆነው ከመሆን ባይዘልም ምጡ በርትቶ እናታችን በወሊድ ምክንያት ከዚህ በላይ መሰቃየት የለባትም፡፡ የማስመሰል ድራማዎች አሁኑኑ መቆም አለባቸው፡፡ የአቢይና ኦሮሙማው አፍዝ አደንግዝ በቀናት ውስጥ ዕልባት ሊያገኝ ይገባል፡፡ እውነተኞቹ ፋኖዎች በሃቀኛ አመራር ትግሉን ዳር ለማድረስ ከተነሱ የኢትዮጵያ ትንሣኤ ግፋ ቢል አሥር ቀናትን ቢፈጅ ነው፡፡ ይህችን መልእክት በምታገኙት የሚዲያ አውታር ሁሉ አሠራጩልኝ፡፡ አደራ፡፡

 

Filed in: Amharic