
ነገሩ እንዲህ ነዉ የህወሃት ሀገወጥ ነጋዴወች የኦፓል ምርቱን ሰወችን ከአሜሪካ እና ከቻይና ድርስ በማስመጣት እዛዉ ወገል ጠና ላይ ሳይቀር ይሸጡታል፡፡ አዲስ አበባ ላይ ዱከም የቻይኖች የኢንዱስተሪ መንደር ዉስጥ አንዱ ትልቁ ህገወጥ ገቢያ የሚካሄድበት ቦታ ነዉ፡፡ የህወሃት ባለሃብቶችና በላስልጣኖች ከቻይናወች ጋር በመደራደር ይሸጡላቸዋል፡፡ ከዱከም የሚወጣ የኢንዱስተሪ ምርት ጋር ተቀላቅሎ የፋብሪካ ምርት ነዉ ተብሎ ይወጣል፡፡ ባንኮክ ሄዶ ኦፓሉ ምርመራ ይደረግለታል፡፡ ከዛም የቻይና እና ህንድ ገቢያ ይቀርባል፡፡ በዚህ መንገድ ህወሃትና ቻይና ተባብረዉ ስማግል አድርገዉ በየ አመቱ ከ 10 ሺህ ኪሎ ግራም በላይ ኦፓል ከሃገር ያወጣሉ፡፡ ይህ እንግዲህ ግብር እንዳይከፈልበት ይሆናል፤ ቆፍረዉ የሚያወጡ ገበሬወች ክፍያ አያገኙም፤ የአማራ ወጣት አይጠቀምም፡፡
ገበሬወችንና ወጣቶችን ሲያስቆፍሯቸዉ የሚዉሉት በደሞዝ ነዉ፡፡ ሙሉ ቀን ሲቆፍር እየዋለ በወር የሚያገኙት ከ 9መቶ እና አንድሽህ ብር አይበልጥም፡፡ የሚሸጠዉ ግን የት እየለሌ ነዉ፡፡ ለምሳሌ ከደላንታ የህወሃት ደላላ 20 ግራም ኦፓል በ 2500 (ሁለት ሺህ አምስት መቶ) ብር ይገዛል፡፡ ዱከም ላይ ለቻይና ባለሃብቶች እንድ ግራም በ 4500 ብር ይሸጣል፡፡ ወገል ጠና ላይ በሁለት ሽህ አምስት መቶ የተገዛዉ 20 ግራም አዲስ አበባ ላይ ለቻይና ባለሃብት ወደ 90 ዘጠና ሺህ ብር ይሸጣል ማለት ነዉ፡፡ አለም ገቢያ ላይ ደግሞ ከ 10ሺህ ዶላር በላይ ይሸጣል፡፡

መፍትሄዉ
——–
ማሽኑን ወጣቶች በነጻ እንዲያስገቡ እና ያመረቱትን ምርት እዚሁ ባህርዳር ላይ እራሳቸዉ አለም አቀፍ ጨረታ እያዘጋጁ እንዲሸጡ፡፡ወጣቶቹና ገበሬዎቹ ተደራጅተዉ እንዲሰሩ ብድር መፍቀድ፤ የኮምቦልጀቻ ቴክኒክ ኮሌጅ ስልጠናዉን እንዲጀምር፡፡ እያንዳንዷ ግራም ኦፓል ተቆጥራ ለክልሉና ለአካባቢዉ ህዝብ ተጠቃሚ የሚሆንበትን መንገድ እንዲመቻች፡፡እኒህን ኮንትሮባንዲስቶች ወጣቱ እራሱ አይቀጡ ቅጣት ቀጥቶ ማጥፋት አለበት ከዛ አካባቢ፡፡ በሰላም ካልወጣ እርምጃ መዉሰድ ነዉ፡፡
ምስሉ ላይ ምታዩት ወጣት እንዲህ ሲቆፍር ዉሎ የቀን ገቢዉ ከ 1 ዶላር በታች ነዉ፡፡ ከድህነት ወለል በታች ማለት ነዉ፡፡ ነገር ግን የምታዩት ምርት አንዷ እንክብል ኦፓል ብቻ በአስር ሺዎች የምትሸጥ ናት፡፡ከዚህም በላይ ለጤና እና ደህንነት አደጋ የተጋለጠ ነዉ፡፡ ያለምንም መከላከያ ነዉ ማእድን እየቆፈረ ያለዉ፡፡
CC/ ANDM CC office ANRS Communication Affairs Office North Wollo RayaKobo Communication Office