>

ብጹእ አቡነ አብርሀም በኮማንድ ፖስቱ "ለጥያቄ"  በሚል ተወሰዱ

በደምሰው ይላቅ
በቅርቡ ከቤምሻንጉል ጉምዝ ተፈናቅለው በባህር ዳር ቅዱስ ጊዬርጊስ ቤተ ክርስቲያን የተጠለሉትን የአማራ ብሄር ተፈናቃዮች የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳደርና የከተማው ነዋሪ እርዳታ እያደረገላቸው ቢሆንም በባህር ዳር የኮማንድ ፖስቱ ዋና አዛዥ ኮሎኔል መሀመድ የሀገረ ስብከቱን ሊቀ ጳጳስ ተፈናቃዮቹን አስወጡ ማለቱን ተከትሎ ብጹእ አቡነ አብርሀም “የእግዚአብሄር ቤት የድሆች መጠጊያ መጠለያ ነው ከዚህ አስወጥቼ ወዴትም ልሰዳቸው አልችልም የት ይወድቃሉ?” በማለታቸው የቤተክርስቲያኗን አስተዳዳሪ ጨምሮ ለጥያቄ ትፈለጋሉ ተብለው ከሰአታት በፊት በመከላከያ ኮማንድ ፖስት ተወስደዋል። ሁኔታውን በቅርብ እየተከታተልን የምናሳውቅ ይሆናል።
Filed in: Amharic