>
5:13 pm - Friday April 19, 2847

«13 ሰው ተገሏል፣ የተቀበሩት 9 ሰዎች ብቻ ናቸው፣ 49 ሰው ቆስሏል፣ 149 ቤት ከእነ ሙሉ እቃው ወድሟል.."- ግን ለምን???

ጌታቸው ሽፈራው ና አቻም የለህ ታምሩ

“ዳኛው ዝንጀሮ መፋረጃው ገደል
ወዴት ላይ ተሁኖ ይነገራል በደል”
* ጠበቆች ወዴት አላችሁ?
~ከቤንሻንጉል ጉምዝ የተፈናቀሉት ወገኖች የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር አላቸው
~ግብር ሲከፍሉበት የነበረው ደረሰኝ አላቸው
~13 ሰው ተገድሏል፣ 49 ሰው ቆስሏል፣ 149 ቤት ተቃጥሏል፣ 23 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ንብረት ወድሟል
~ከ2000 በላይ ሰዎች ከሞቀ ቤታሰቸው ተፈናቅለው ለ7 ወር ጎዳና ላይ ወድቀዋል
~ከተፈናቀሉት 527 አባውራና እማውራዎች መካከል  መረጃዎቻቸው የተገኘው የ340 ነው። ቀሪዎቹ የት እንደገቡ አይታወቅም። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ወደ ባህርዳር በመጡበት ወቅት ብአዴን ከ150 በላይ የሚሆኑትን በመኪና ጭኖ የት እንዳደረሳቸው አይታወቅም። ስልካቸውም አይሰራም!
~እነዚህ ወገኖች በርካታ የመብት ጥሰቶች ተፈልመውባቸዋል።  የሚከራከርላቸው ወገን  ግን አላገኙም። ይህን በርካታ ጥሰት ጠበቆች ሊይዙት ይገባ ነበር። አሁንም ጊዜ አለ። መንግስት በዘር ማፅዳት መከሰስ አለበት።
~ይህ ጉዳይ በፍርድ ቤት ሲያዝ በዘመኑ ፍርድ ቤቶች ፍትሕ ይገኛል ተብሎ አይደለም። አይገኝም። ነገር ግን ፍርድ ቤት ቀርበው በገዥዎቹ ላይ ምስክር የሚሆኑት የጎጅዎቹ ናቸው።  ተፈናቃዮቹ የተፈፀመውን ሁሉ በዝርዝር ለመናገር ትልቅ አጋጣሚ ያገኛሉ። ጉዳዩ ለሚዲያ በእጅጉ ቅርበት ይኖረዋል። ፍርድ ቤቱ  የመታገያም መድረከ መሆን ይችላል፣ የበደል መግለጫ ይሆናል!  አይደለም ይህን ያህል ወንጀል ቀርቶ የበደል ትንሽ የለውምና ተፈናቃዮቹና ጠበቆቻቸው የሚያቀርቧቸው መረጃዎች ትልቅ አስተዋፅኦ አላቸው! የዛሬውን ሳይሆን ያለፉትንም ጭምር ለማጋለጥ   ያግዛሉ!
በመሆኑም  ለጉዳዩ ተቆርቋሪ የሆኑ ጠበቆች ተፈናቃዮቹ ያላቸውን በርካታ ማስረጃ አሰባስበው መንግስትን ሊከሱት ይገባል! ይህ ሲሆን ፌስቡክ ላይ ከሚለጠፈው፣ አንድ ቀን በራዲዮ ከሚነገረው የጠቀመ ስራ ይሰራል! በቀጣይ ገዥዎችን ለፍትህ ለማቅረብም አንድ ጅምር ይሆናል!
* ቀሳውስቱንም አሳደዷቸው!
የተረጋገጠ የመሬት  ይዞታ እያላቸው፣ የመሬት ግብር እየከፈሉ የተባረሩበት ሰበብ አንድ ሰው በመገደሉ ነው። ቀሳውስት የሚያስተምሩት የእግዚያብሔርን ቃል ነው። ከቃሉ ዋነኛው ደግሞ “አትግደል” ነው። ሆኖም ግብር ሲያስከፍላቸው የኖረው የቤንሻንጉል ክልል መንግስት ቀሳውስቱ ለሚቃወሙት ወንጀል በጅምላ ተጠያቂ አደረጋቸው። እናቶችን፣ ህፃናትን፣ ምስኪን ገበሬዎችን በጅምላ እንዳባረረው ቀሳውስትንም አሳደዳቸው። እንደ እግዚያብሔር ፈቃድ ሆኖ ህይወታቸውን ተርፏል።
በምስሉ የሚታዩት ቄስ እንኳሆነ ቸሬ ይባላሉ። በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ከማሽ ዞን ጅንጋፎይ ወረዳ፣ በለው ደዲሳ ቀበሌ የሚገኘው ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስትያን ኃላፊ ነበሩ። በግል ፀብ ምክንያት “ሰው ተገደለ” ተብሎ በጅምላ ከ2000 በላይ ሕዝብ ሲባረር የቅድስ ገብርኤሉን ኃላፊ ቄስም አሳድደዋቸዋል።
ቄስ እንኳሆነ ቼሬ  ሜዳ ላይ ከወደቁትና በአሁኑ ወቅት የጤና እክል ከገጠማቸው ተፈናቃዮች መካከል ናቸው። ከቄስ እንኳሆነ በተጨማሪ ሌሎች 14 ቀሳውስትንም አሳድደዋቸዋል። “አትግደል” እያሉ ከሚያስተምሩበት ደብር ከተፈናቀሉት ቀሳውስት መካከል:_
1) ቄስ እንኳሆነ ቼሬ
2)ቄስ ምንአለ አያሌው
3) ቄስ ጎጃም በየነ
4) ቄስ ውበቱ እንየው
5)ቄስ አዲስ አንተነህ
6)ቄስ በለጠ ንጉሴ
7)ቄስ መንክር ውቤ
8ኛ )ቄስ ጫኔ ታደሰ
9) ቄስ ሀብታሙ ሽበሽ
10)ቄስ አደመ መኮንን
11)ቄስ የሽዋስ የኋላው
12)ቄስ ላቀው መንግስቴ
13)ቄስ ስልጣኑ ከፍአለ
14)ቄስ አበበ በእውቀቱ
15)ቄስ አበበ መልሰው ይገኙበታል።
 ሌሎች በስም ያልተጠቀሱ ቀሳውስትም እንደተፈናቀሉ ለማወቅ ተችሏል
              #####
አቻምየለህ ታምሩ
ከመተከል የተፈናቀሉ አማሮች  ለጠቅላይ ሚንስትሩ ያቀረቡት አቤቱታ!
*«በኖርንበት አመት ውስጥ ከአምስት ጊዜ በላይ ተደጋጋሚ ጥቃት ሲደርስብን ቆይቷል።»
*«የአማራ ክልል መንግሥት» የቤንሻምጉል ጉምዝ ነዋሪዎች እንጅ የእኔ አይደላችሁም ብሎናል»
*«13 ሰው ሞቷል፣ የተቀበሩት 9 ሰዎች ብቻ ናቸው፣ 49 ሰው ቆስሏል፣ 149 ቤት ከእነ ሙሉ እቃው ወድሟል፣ በአጠቃላይ ከ23 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ወድሟል።»
______________________________
የሚከተለው ተፈናቃዮቹ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ያቀረቡት አቤቱታ ነው።
ሚያዝያ 15 ቀን 2010 ዓም
ለጠቅላይ ሚ/ር ፅ/ቤት
አዲስ አበባ
አቤቱታ አቅራቢዎች ከቤንሻንጉል ጉምዝ ከማሽ ዞን ከበለው ጅጋንፎይ ወረዳ በለው ደዴሳ ቀበሌ ስንሆን ከቤንሻንጉል ጉምዝ የተፈናቀልን 527 የምንሆን አባውራ ብቻ ቤተሰብን ሳይጨምር ታግተኝ እንገኛለን።
እኛ ብዛታችን ከላይ የተጠቀሰው አባውራዎች ከ1992 ዓም ጀምሮ እስከ 2010 ዓም ድረስ በክልሉ ውስጥ ኑረናል። በኖርንበት አመት ውስጥ ከአምስት ጊዜ በላይ ተደጋጋሚ ጥቃት ሲደርስብን ቆይቷል። ለመጥቀስ ያህል በ1995 ዓም ካለንበት ቦታ ተፈናቅለን በጥረታችን ደክመን ያፈራነው ሀብታችን የተዘረፍን ሲሆን በ2000 ዓም የድብደባ እና የዘረፋ ወንጀል ተፈፅሞብናል።
በ2003 ዓም በላባችን ያፈራነው ሀብት ተዘርፎ ቤታችን ተቃጥሎ ተባርረን በቡሬ ወረዳ ሰፍረን ከቆየን በኋላ የአማራ ክልል መንግስት ከቤንሻንጉል ክልል መንግስት ጋር በመነጋገር ወደነበርንበት ተመልሰን እንድንቀመጥ ተደርጎ ነበር።
አሁንም ጥቅምት 17/2010 ዓም በሰው ሕይወትና ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶብናል። ህይወታቸው የተቀጠፈው 13 ሰዎች ሲሆኑ ስርዓተ ቀብራቸው የተፈፀመው የ9 ሰዎች ብቻ ነው። 4 ሰዎች ግን በውሃ ጉድጓድ ውስጥ ገብተው አስከሬናቸውን ማውጣት አልተቻለም። በክብር ለመቅበር ካልበቁት በተጨማሪ በቀስትና በጦር ተወግተው የቆሰሉ 49 ሰዎች የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።149 ቤቶች ከእነ ሙሉ ንብረታቸው የወደሙ ሲሆን ከቁም ከብት ጀምሮ፣ የማይንቀሳቀስ ንብረት እንዲሁም ሳይሰበሰብ ከቀረው ሰብል ጋር ባጠቃላይ የጠፋው ንብረት ድምር 23 ሚሊዮን ብር የሚሆን ወድሞ ቀርቷል።
እኛ በደሉ ከተፈለመብን ቀን ጀምሮ ቦታውን በመልቀቅ ወደ አማራ ክልል መግባታችን ቢታወቅም የአማራ ክልል መንግስት ግን አቤቱታችን ሳይቀበል ቸል በማለት “እናንተኮ የቤንሻምጉል ጉምዝ ነዋሪዎች እንጅ የእኔ ሕዝቦች አይደላችሁም። ስለዚህ የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልልን ጠይቁ” በማለት ባለመቀበሉ እየተሰቃየን እንገኛለን። በመሆኑም የወደቅንበት ቦታ እና የጠፉብንን ንብረቶች ከግምት ውስጥ በመክተት አፋጣኝ የሆነ መፍትሔ እንዲሰጠን ስንል በትህትና እንጠይቃለን።
አመልካቾች
1)ቄስ ምንአለ አያሌው (የቤተሰብ ብዛት 8
2)ዋሴ ጥላሁን (የቤተሰብ ብዛት 5
3) ተስፋየ ዋለ (6
4) ምን አለ ተሾመ (የቤተሰብ ብዛት 3)
5) ድረስ ታረቀኝ (የቤተሰብ ብዛት 4)
6) አእምሮ ተገኘ (የቤተሰብ ብዛት 5)
7) አዱኛ ታረቀኝ (የቤተሰብ ብዛት 8)
8) ይልቃል መኮንን (የቤተሰብ ብዛት 6)
9) የስጋ ሽበሽ (የቤተሰብ ብዛት 5)
10) አንተነህ ምስሌ (የቤተሰብ ብዛት 4)
11) ቄስ ጎጀም በየነ (የቤተሰብ ብዛት 7
12) ቄስ ውበቱ እብየው (የቤተሰብ ብዛት 3)
13) ታገለ ፈንቴ (የቤተሰብ ብዛት 3)
14) ገሬ አወቀ (የቤተሰብ ብዛት 3)
15) ጌታነህ ሽፈራው (የቤተሰብ ብዛት 3)
16) ተሾመ ደረሰ (የቤተሰብ ብዛት 5)
17) አለማየሁ ዋለ (የቤተሰብ ብዛት 2)
18) ዘላለም ዋሴ (የቤተሰብ ብዛት 2)
19) እንቻለው አበበ (የቤተሰብ ብዛት 6)
20) በቃል እንቻለው (የቤተሰብ ብዛት 2)
21) ቄስ አዲስ አንተነህ (የቤተሰብ ብዛት 5)
22) አስሜ ሽበሽ (የቤተሰብ ብዛት 2)
23) ማናዬ ገዳሙ (የቤተሰብ ብዛት 3)
24) ዘላለም አየለ (የቤተሰብ ብዛት 3)
25) ዘሪሁን ቸኮል (የቤተሰብ ብዛት 5)
26) ፈንታሁን አዳሙ (የቤተሰብ ብዛት 4)
27) ምህረቴ ታረቀኝ (የቤተሰብ ብዛት 3)
28) ቢሻው ታረቀኝ (የቤተሰብ ብዛት 2)
29) ምግባሩ ታረቀኝ (የቤተሰብ ብዛት 2)
30) ባንቹ ታረቀኝ (የቤተሰብ ብዛት 2)
31) ይስማው ብርሃኑ (የቤተሰብ ብዛት 2)
32) አበበ ብርሃኑ (የቤተሰብ ብዛት 2)
33) አንተነህ ወርቄ (የቤተሰብ ብዛት 4)
34) ይሳላል ስንሻው (የቤተሰብ ብዛት 2)
35) አትርሳው አደላ (የቤተሰብ ብዛት 2)
36) ይልቃል ያለው (የቤተሰብ ብዛት 2)
37) እንግዳው ምስሌ (የቤተሰብ ብዛት 2)
38) አሰሙ እንዳለው (የቤተሰብ ብዛት 6)
39) አየነው አለኸኝ (የቤተሰብ ብዛት 2)
40) ወንድሙ አወቀ (የቤተሰብ ብዛት 3)
41) ሸጋው ስንሻው ( የቤተሰብ ብዛት 3)
42) መልካሙ ገደፍ (የቤተሰብ ብዛት 4)
43) እንዳሻው አንተነህ (የቤተሰብ ብዛት 2)
44) ልቅናው ኑሬ (የቤተሰብ ብዛት 2)
45) ቀሬ አንዱዓለም (የቤተሰብ ብዛት 2)
46) ሙጬ ደረሰ (የቤተሰብ ብዛት 2)
47) ሻሼ ይልቃል (የቤተሰብ ብዛት 2)
48) ጎዳናው አጥናፍ (የቤተሰብ ብዛት 2)
49) ያሳቡ ደሴ (የቤተሰብ ብዛት 5)
50) የሽዋስ ይሁን (የቤተሰብ ብዛት 2)
51) ስራ መኮንን (የቤተሰብ ብዛት 6)
52) አበዛ አስሬ (የቤተሰብ ብዛት 3)
53) ይረፍ እንየው (የቤተሰብ ብዛት 3)
54) ቢተው ጥላ (የቤተሰብ ብዛት 2)
55) አጃናው ከበደ (የቤተሰብ ብዛት 4)
56) ገበየሁ አበበ (የቤተሰብ ብዛት 3)
57) ቢተው ከበደ (የቤተሰብ ብዛት 3)
58) አጥናፍ አልማው (የቤተሰብ ብዛት 2)
59) ገበያው አበበ (የቤተሰብ ብዛት 2)
60) ሁነኛው በለጠ (የቤተሰብ ብዛት 6)
61) አለኸኝ አንዱዓለም (የቤተሰብ ብዛት 6)
62) ቸኮል አለኸኝ (የቤተሰብ ብዛት 4)
63) መልካሙ አለኸኝ (የቤተሰብ ብዛት 2)
64) አያልነህ አስማረ (የቤተሰብ ብዛት 5)
65) ታምር አስማረ (የቤተሰብ ብዛት 5)
66) ደመላሽ ሁነኛው (የቤተሰብ ብዛት 6)
67) መለሰ ሁነኛው (የቤተሰብ ብዛት 5)
68) ልቅና ጥላሁን (የቤተሰብ ብዛት 5)
69) ላቀ አልማው (የቤተሰብ ብዛት 6)
70) ፈንታሁን አጥናፍ (የቤተሰብ ብዛት 3)
71) አንጓች አለኸኝ (የቤተሰብ ብዛት 2)
72) ጌታቸው አበባው (የቤተሰብ ብዛት 3)
73) አንሙት ተሾመ (የቤተሰብ ብዛት 3)
74) ፈንታሁን አሻግሬ (የቤተሰብ ብዛት 4)
75) ጌትነት አሻግሬ (የቤተሰብ ብዛት 2)
76) አስሜ ጥላዬ (የቤተሰብ ብዛት 5)
77) አልማው ጥላዬ (የቤተሰብ ብዛት 3)
78) ሹመቴ ጥላዬ (የቤተሰብ ብዛት 2)
79) ታደሰ ልመንህ (የቤተሰብ ብዛት 2)
80) ይልቃል ታደሰ (የቤተሰብ ብዛት 4)
81) ጎጃም ጌታነህ (የቤተሰብ ብዛት 2)
82) አዲሱ አሳሴ (የቤተሰብ ብዛት 2)
83) አዲሴ ሞላ (የቤተሰብ ብዛት 3)
84) አራጌ ስሜነህ (የቤተሰብ ብዛት 3)
85) ይፍረደው ታደሰ (የቤተሰብ ብዛት 2)
86) በላይነህ ሻረው (የቤተሰብ ብዛት 4)
87) እማሆይ አጀቡሽ (የቤተሰብ ብዛት 4)
88) አያልነህ ከበደ (የቤተሰብ ብዛት 5)
89) አብርሃም ሞላ (የቤተሰብ ብዛት 9)
90) የሀሳብ ሞላ (የቤተሰብ ብዛት 6)
91) ጊዜው ጥላሁን (የቤተሰብ ብዛት (4)
92) ማማር ጥላሁን (የቤተሰብ ብዛት 4)
93) አሸብር የኔውብ (የቤተሰብ ብዛት 3)
94) ታንቴ ገበየሁ (የቤተሰብ ብዛት 3)
95) እሸቴ ፀጋ (የቤተሰብ ብዛት 8)
96) አንተነህ ፀጋ (የቤተሰብ ብዛት 4)
97) እየሩስ ተሜ (የቤተሰብ ብዛት 3)
98) ሞላ ሽፈራው (የቤተሰብ ብዛት 4)
99) መልካሙ አስቻለው (የቤተሰብ ብዛት 2)
100)ሙሉ አስማረ (የቤተሰብ ብዛት 2)
101) ባንቹ ታረቀኝ (የቤተሰብ ብዛት 2)
102) ሁነኛው ጥላሁ (የቤተሰበ ብዛት 4)
103) ሰርጎ ምንውዬ (የቤተሰብ ብዛት 3)
104) የሽዋስ ሽፈራው (የቤተሰብ ብዛት 3)
105) አንሙት ካሴ (የቤተሰብ ብዛት 2)
106) ይልቃል ደለለ (የቤተሰብ ብዛት 2)
107) ተሜ አዳሙ (የቤተሰብ ብዛት 4)
108) ያሬድ ደምስ (የቤተሰብ ብዛት 2)
109) ቄስ በለጠ ንጉሴ (የቤተሰብ ብዛት 3)
110) ፈጠነ ልየው (የቤተሰብ ብዛት 3)
111) ፈንታሁን ልየው (የቤተሰብ ብዛት 8)
112) ካሳሁን ብዙነህ (የቤተሰብ ብዛት 6)
113) አሰፋ ገበየሁ (የቤተሰብ ብዛት 3)
114) ምግባር በቀለ (የቤተሰብ ብዛት 3)
115) ዋጋ በቀለ (የቤተሰብ ብዛት 3)
116) ባንቹ በቀለ (የቤተሰብ ብዛት 2)
117) ልቡሞኝ አሞኜ (የቤተሰብ ብዛት 3)
118) ገብሬ ሽመልስ (የቤተሰብ ብዛት 3)
119) መንገሽ አያሌው (የቤተሰብ ብዛት 3)
120) አለነ ጌትነት (የቤተሰብ ብዛት 2)
121) ምትኩ አለነ (የቤተሰብ ብዛት 3)
122) ካሴ አጥናፍ (የቤተሰብ ብዛት 3)
123) ካሴ እሼቴ (የቤተሰብ ብዛት 2)
124)ዝግጅ ተፈራ (የቤተሰብ ብዛት 3)
125) ምህረት ገበየሁ (የቤተሰብ ብዛት (2)
126) ስፍራሽ ከልካይ (የቤተሰብ ብዛት 6)
127) ዘላለም ፈንታሁን (የቤተሰብ ብዛት 4)
128) አገር ደምስ (የቤተሰብ ብዛት 2)
129) አብሬ መንግስት (የቤተሰብ ብዛት 2)
130) ተመልከት ደምስ ( የቤተሰብ ብዛት 2)
131) አበባው ፈንቴ (የቤተሰብ ብዛት 3)
132) ጌትነት ተስፋ (የቤተሰብ ብዛት 2)
133) አያሌው መንግስቴ (የቤተሰብ ብዛት 5)
134) ፈጠነ ዘላለም (የቤተሰብ ብዛት 2)
135) ገረመው መንግስቴ (የቤተሰብ ብዛት 2)
136) ይሁኔ ደሴ (የቤተሰብ ብዛት 3)
137) ማናዬ እንየው (የቤተሰብ ብዛት 2)
138) አሰፋ እንየው (የቤተሰብ ብዛት 2)
139) ተስፋዬ እውነቴ (የቤተሰብ ብዛት 3)
140) ዘላለም ፈንታሁን (የቤተሰብ ብዛት 4)
141) በለጠ ወርቄ (የቤተሰብ ብዛት 2)
142) ዳኝዬ እንደሻው (የቤተሰብ ብዛት 3)
143) ሀይሉ ደመቀ (የቤተሰብ ብዛት 3)
144) ጌቴ ደምሰው (የቤተሰብ ብዛት 2)
145) አራጋው አለሙ (የቤተሰብ ብዛት 2)
146) በላይነህ ፀሀይ (የቤተሰብ ብዛት 2)
147) አያሌው በላይ (የቤተሰብ ብዛት 3)
148) በልእስቲ ቃሌ (የቤተሰብ ብዛት 2)
149) ሰው መሆን የሻነህ ( የቤተሰብ ብዛት 2)
150) ቄስ መንክር ውቤ (የቤተሰብ ብዛት 4)
151) ስማቸው ታደሰ (የቤተሰብ ብዛት 2)
152) ተረፈ አክሉሊ (የቤተሰብ በዛት 5)
153) ምስጋና ምናሉ (የቤተሰብ ብዛት 2)
154) ዘመን አዲስ (የቤተሰብ ብዛት 6)
155) አበባው አማረ (የቤተሰብ ብዛት 4)
156) ቄስ ጫኔ ታደሰ (የቤተሰብ ብዛት 6)
157) አወ እስከዚያው (የቤተሰብ ብዛት 4)
158) ቄስ ሀብታም ሽበሽ (የቤተሰብ ብዛት 5(
159) አዲስ ደምልለው ( የቤተሰብ ብዛት 2)
160) ዘሪሁን በላይ (የቤተሰብ ብዛት 6)
161) ባለው በላይ (የቤተሰብ ብዛት 5)
162) በለጥ ደረጀ (የቤተሰብ ብዛት 3)
163) አበባው መኮንም (የቤተሰብ ብዛት 6)
164) ጓዱ መኮንን (የቤተሰብ ብዛት 3)
165) ይርሴ እንግዳ (የቤተሰብ ብዛት 3)
166) ሽብሬ ጌትነት (የቤተሰብ ብዛት 3)
167) ምህረት ገበየሁ (የቤተሰብ ብዛት 2)
168) ዜና አያልነህ (የቤተሰብ ብዛት 2)
169) ገበያው ሞላ (የቤተሰብ ብዛት 3)
170) አጥናፍ አልማው (የቤተሰብ ብዛት 4)
171) ወርቅነህ ወንዴ (የቤተሰብ ብዛት 2)
172) ዘበነ ስንታየሁ (የቤተሰብ ብዛት 3)
173) አትንኩት ስንታየሁ (የቤተሰብ ብዛት 2)
174) ፈጠነ ዘላለም (የቤተሰብ ብዛት 2)
175) ደረጀ ግዛቸው (የቤተሰብ ብዛት 2)
176) ቻሌ አለኸኝ (የቤተሰብ ብዛት 3)
177) ስሜ ተፈራ (የቤተሰብ ብዛት 5)
178) ደጀኔ አንዱዓለም (የቤተሰብ ብዛት 4)
179) ደጌ አይነኩሉ (የቤተሰብ ብዛት 3)
180) ወርቅነህ አድምጥ (የቤተሰብ ብዛት 3)
181) ወርቅነህ ጫኔ ( የቤተሰብ ብዛት 2)
182) ቄስ አደመ መኮንን (የቤተሰብ ብዛት 2)
183) አበበ መኮንን (የቤተሰብ ብዛት 4)
184) ሀብቴ ታደሰ (የቤተሰብ ብዛት 4)
185) ሙሉሰው አለኸኝ (የቤተሰብ ብዛት 2)
186) አብሬ መንግስቴ ( የቤተሰብ ብዛት 3)
187) ጥላሁን አንተነህ (የቤተሰብ ብዛት 3)
188) መስፍን የኋላው (የቤተሰብ ብዛት 3)
189) መኬ የኋላው (የቤተሰበ ብዛት 2)
190) አብዮት የኋላው (የቤተሰብ ብዛት 3)
191) ቄስ የሽዋስ የኋላው (የቤተሰብ ብዛት 3)
192) ማመን አበረ (የቤተሰብ ብዛት 3)
193) ስንቴ ሞላ (የቤተሰብ ብዛት 2)
194) ስሜነህ አበበ (የቤተሰብ ብዛት 2)
195) ሀይማኖት ተሾመ (የቤተሰብ ብዛት 3)
196) አበበ ጌትነት (የቤተሰብ ብዛት 2)
197) ኑሬ አያሌው (የቤተሰብ ብዛት 2)
198) አደራው ምስጋናው (የቤተሰብ ብዛት 3)
199) ጥበብ በላይነህ (የቤተሰብ ብዛት 2)
200) ተስፋዬ ወንድም (የቤተሰብ ብዛት 2)
201) መለሰ ተመስገን (የቤተሰብ ብዛት 3)
202) ጠጋው ወንድም (የቤተሰብ ብዛት 4)
203) አያሌው መንግስቴ (የቤተሰብ ብዛት 4)
204) ቄስ ላቀው መንግስቴ (የቤተሰብ ብዛት 3)
205) ስሌ ሁነኛው (የቤተሰብ ብዛት 4)
206) ድረስ እንየው (የቤተሰብ ብዛት 3)
207) በላይነህ ከፍያለው (የቤተሰብ ብዛት 3)
208) ነጋ አለባቸው (የቤተሰብ ብዛት 4)
209) ገደፋው ወርቁ (የቤተሰብ ብዛት 8)
210) አድማስ ኑሬ (የቤተሰብ ብዛት 2)
211) በርነሽ በላቸው ( የቤተሰብ ብዛት 3)
212) ጥበቡ አለባቸው (የቤተሰብ ብዛት 4)
213) ካሳ መኩሪያ (የቤተሰብ ብዛት 2)
214) የሽዓለም ዘላለም (የቤተሰብ ብዛት 2)
215) አያሌው በላይ (የቤተሰብ ብዛት 4)
216) ሽቱ ስማቸው (የቤተሰብ ብዛት 3)
217) ፈጠነ ዳኘ (የቤተሰብ ብዛት 2)
218) ምትኩ አረጋ (የቤተሰብ ብዛት 5)
219) ቄስ ስልጣኑ ከፍአለ (የቤተሰብ ብዛት 6)
220) ትዕዛዙ በላይ (የቤተሰብ ብዛት 2)
221) ውቤ እንየው (የቤተሰብ ብዛት 3)
222) ዘውዱ እሸቴ ( የቤተሰብ ብዛት 3)
224) አለማየሁ ዝጋለ (የቤተሰብ ብዛት 3)
225) አበባው ደመላሽ (የቤተሰብ ብዛት 4)
226) አዲሱ በይህ (የቤተሰብ ብዛት 4)
227) አንሙት ከፍ አለ (የቤተሰብ ብዛት 6)
228) አስቻለ ከፋለ (የቤተሰብ ብዛት 3)
229) በሪሁን ይርዴ (የቤተሰብ ብዛት 2)
230) ይበሉ ይዘንጋው (የቤተሰብ ብዛት 3)
231) አለምቀር አናጋው (የቤተሰብ ብዛት 2)
232) ታበሩ በላይ ( የቤተሰብ ብዛት 4)
233) ገደፋው ሞላ (የቤተሰብ ብዛት 6)
234) ስሜ ሞላ (የቤተሰብ ብዛት 3)
235) አዳም ከፍ አለ (የቤተሰብ ብዛት 6)
236) ቄስ አበበ መልሰው (የቤተሰብ ብዛት 4)
237) ቄስ አበበ በውቀት (የቤተሰብ ብዛት 4)
238) ትግስት ሙሉ (የቤተሰብ ብዛት 2)
239) አሳቤ ቀሬ (የቤተሰብ ብዛት 4)
240) ንብረት ቀሬ (የቤተሰብ ብዛት 3)
241) አይቸው ወንድም (የቤተሰብ ብዛት 4)
242) መላኩ ጌትነት (የቤተሰብ ብዛት 3)
243) አዲሱ ሙጬ (የቤተሰብ ብዛት 3)
244) ይታይህ መኮንን (የቤተሰብ ብዛት 7)
245) ብርሃኑ ስሜነህ (የቤተሰብ ብዛት 2)
246) ባይህ ታፈረ (የቤተሰብ ብዛት 5)
247) ይመር የኋላሸት (የቤተሰብ ብዛት 5)
248) ባህሩ ባይህ ( የቤተሰብ ብዛት 3)
249) ሀብታሙ ሙጬ (የቤተሰብ ብዛት 4)
250) ያየህ መኩሪያ (የቤተሰብ ብዛት 2)
251) አማረ አያና (የቤተሰብ ብዛት 5
252) ፈንቴ ካሳ (የቤተሰብ ብዛት 4)
253) ሞትባይኖር አንዱዓለም (የቤተሰብ ብዛት 4)
254) ኔሬ ተፈራ (የቤተሰብ ብዛት 5)
255) ብርሌው ሞላ (የቤተሰብ ብዛት 4)
256) ልመንህ መኩሪያ (የቤተሰብ ብዛት 5)
257) ሙሉቀን አናጋው (የቤተሰብ ብዛት 2)
258) ያየህ ሞሌ (የቤተሰብ ብዛት 2)
259) የሺበላይ ዘውዱ (የቤተሰብ ብዛት 3)
260) የኔሰው ሞሴ (የቤተሰብ ብዛት 4)
261) ደሴ በየነ (የቤተሰብ ብዛት 4)
262) ይታያል አናጋው (የቤተሰብ ብዛት 3)
263) ግራማች ባብል (የቤተሰብ ብዛት 2)
264)ሙሉጌታ ዳኘው (የቤተሰብ ብዛት 3)
265) ሙሉነህ ወርቁ (የቤተሰብ ብዛት 4)
266) ደሴ የኔሰው ( የቤተሰብ ብዛት 2)
267) ዳኘው ጠብቀው (የቤተሰብ ብዛት 5)
268) መለስ ጥላሁን (የቤተሰብ ብዛት 3)
269) በርሄ የኔሰው (የቤተሰብ ብዛት 2)
270) ሞሴ ሰውኔ (የቤተሰብ ብዛት 3)
271) መልካሙ ታምሩ (የቤተሰብ ብዛት 2)
272) እታጓድ አለነ (የቤተሰብ ብዛት 2)
273) ዳኘ አበባው (የቤተሰብ ብዛት 3)
274) ትግስት ሙሉ (የቤተሰብ ብዛት
275)ሽመልስ ሙሉጌታ (የቤተሰብ ብዛት 2)
276) አንማው ተስፋዬ (የቤተሰብ ብዛት 2)
277) የኔሰው ምናዬ (የቤተሰብ ብዛት 4)
278) ንብረት በቀለ (የቤተሰብ ብዛት 3)
279) አንሙት እስተዚያ (የቤተሰብ ብዛት 2)
280) ያሳቡ ወንድም (የቤተሰብ ብዛት 2)
281) ታፈረ ወንድም (የቤተሰብ ብዛት 2)
282) ንብረት አበባው (የቤተሰብ ብዛት 3)
283) አስሜ አጉማዝ (የቤተሰብ ብዛት 2)
284) የኔነህ መኩሪያ (የቤተሰብ ብዛት 3)
285) አሳየ አበባው (የቤተሰብ ብዛት 2)
286) የኔሆድ ሞላ (የቤተሰብ ብዛት 2)
287) መኩሪያ ብሬሰው (የቤተሰብ ብዛት 2)
288) ታዘብ መኮንን (የቤተሰብ ብዛት 4)
289) ካሴ አለባቸው (የቤተሰብ ብዛት 2)
290) የሮም ቢተው (የቤተሰብ ብዛት 4)
291) ሞሴ አራጋው (የቤተሰብ ብዛት 5)
292) ሞኞ ጓዴ (የቤተሰብ ብዛት 6)
293) መሰረት የኔሁን (የቤተሰብ ብዛት 5)
294) ብርሃን ጋሻው ( የቤተሰብ ብዛት 3)
295) መለሰ ቸኮል (የቤተሰብ ብዛት 4)
296) አሳቡ አያና (የቤተሰብ ብዛት 3)
297) ጌታሰው አራጋው (የቤተሰብ ብዛት 3)
298) ዘሩ ወንዲፈወራው (የቤተሰብ ብዛት 2)
299) ሞሌዋ ዳኛው (የቤተሰብ ብዛት 2)
300) አስማረ ተስፋ (የቤተሰብ ብዛት 4)
301) ምህረቴ አንሙት (የቤተሰብ ብዛት 2)
302) በለጠ በቀለ (የቤተሰብ ብዛት 3)
303) አንዱዓለም ጋሻው (የቤተሰብ ብዛት 2)
304) መልኬ አራጋው (የቤተሰብ ብዛት2)
305) አሞኘ ክንዴ (የቤተሰብ ብዛት 2)
306) አንዱዓለም ጥላሁን (የቤተሰብ ብዛት 3)
307) ወይንጉስ ቢምረው (የቤተሰብ ብዛት 2)
308) አጠደ ቸኮል (የቤተሰብ ብዛት 2)
309) አለኸኝ አስራ (የቤተሰብ ብዛት 3)
310) አዝመራው አማኔ (የቤተሰብ ብዛት 2)
311) ሀብቴ ቸኮል (የቤተሰብ ብዛት 2)
312) ነበረ አስራት (የቤተሰብ ብዛት 2)
313) በልስቲ ብዙዬ (የቤተሰብ ብዛት 2)
314) መኳንንት ምንውዬ (የቤተሰብ ብዛት 2)
315) አየነው ተሰማ (የቤተሰብ ብዛት 3)
316) አበበ ተግባር (የቤተሰብ ብዛት2)
317) ባንችግዜ ጋሹ (የቤተሰብ ብዛት 2)
318) አቶ ይታይህ (የቤተሰብ ብዛት 2)
319) ገበያው ብርሃኑ (የቤተሰብ ብዛት 2)
320) ፈለጉ ባሳዝነው (የቤተሰብ ብዛት 4)
321) ማስቴ ስማቸው (የቤተሰብ ብዛት 3)
322) አበበ ገበያው (የቤተሰብ ብዛት 5)
323)ሀብቴ ሞላ (የቤተሰብ ብዛት 4)
324) አንሙት አጥናፍ (የቤተሰብ ብዛት 4)
325) ብርሃኑ አይናለም (የቤተሰብ ብዛት 2)
326) ማስረሻ ቤነ (የቤተሰብ ብዛት 6)
327) ዳኛው ስመኝ (የቤተሰብ ብዛት 5)
328) ቻላቸው ጋሻው (የቤተሰብ ብዛት 2)
329) ውቤ በላይነህ (የቤተሰብ ብዛት 3)
330) ምናለ ታምሩ (የቤተሰብ ብዛት 2)
331) ጌታሰው ብርሃኔ (የቤተሰብ ብዛት 2)
332) ክብረት ጋሻዬ (የቤተሰብ ብዛት 3)
333) ሀይለሌ ልየው (የቤተሰብ ብዛት 5)
334) ጥላዬ ባይለየኝ (የቤተሰብ ብዛት 5)
335)አወቀ ባይለየኝ (የቤተሰብ ብዛት 3)
336) ይናገር በለጠ (የቤተሰብ ብዛት 4)
337) ተስፋዬ ግዛቸው (የቤተሰብ ብዛት 2)
338) ስጦታው መሰረት (የቤተሰብ ብዛት 2)
339)ተስፋዬ አወቀ (የቤተሰብ ብዛት 3)
340) ጊዜ አወቀ (የቤተሰብ ብዛት 3)
Filed in: Amharic