ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ ነው። መልሶችን በውሸት የሚያጅል፣ ከሰውነቱ ይልቅ ብሄሩን የሚያልቅ፣ የፀጥታ ሀይሉ እርምጃ እንዲወስድ አምባገነናዊ ትእዛዝ የሚሰጥ፣ አለመያዝ እንጂ ስርቆት ስራ ነው የሚል፣ በሸፍጥና ሽንሸና ፖለቲካ የተካነ፣ ከአንድ ዘር ሰራዊት ያዋቀረ፣ ያለጥፋት ዜጎችን ማሰር እንጂ መፍታት የማያውቅ፣ ሞቶ እንኳ በጠባቂ ከሙታን ያልገጠመ…
ጠቅላይ ሚንስትር ሀይለማርያም ነው። የሙት መንፈስ ታቅፎ ሲዞር ስድስት አመት የደነዘዘ፣ ገዳዮችን ሲያወድስ አልሞ ተኳሾችን ሲያቆለጳጵስ የከረመ፣ ከበታቾቹ ትዛዝ ለመቀበል ወደኋላ ያላለ፣ ለህዝብ ሳይሆን ለሃያ አራት የወያኔ ሌቦች ጥቅም የቆም፣ የህዝብን ሀይል መረዳት የተሳነው…

መቶ ሚሊዮኖች በአገራቸው ጉዳይ እኩል እንዲሆኑ የውሀልኩን ያስተካከል መሀንዲስ፣ ባገሬ ጉዳይ እኔ ከእገሌ አልበልጥምን የሰበከ ሀዋርያ ለኔ ጠቅላይ ሚንስትር አይደለም! አብይ አብይ ነው! አብይ!