>

ዶክተር ብርሃኑ ነጋ " አሸባሪ! ወንበዴ ! " እየተባለ በተሰደበበት ፓርላማ "አንቱ" እየተባለ ሲሞካሽ ዋለ!!!

ዶክተር ብርሃኑ ነጋ  ” አሸባሪ ! ” ወንበዴ ! ” እየተባለ በተሰደበበት ፓርላማ “አንቱ ” እየተባለ  ሲሞካሽ ዋለ!!!

ቬሮኒካ መላኩ
1~ ከባለፈው ሳምንት ጀምሮ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ከዚህ በኋላ መረን የለቀቀ የህውሃትን መግለጫ  እንዳያቀርብ ቀጭን ትእዛዝ ተሰጥቶታል። ህውሃቶችም ይሄን አውቀው ነው መሰለኝ በትግራይ ቴሌቪዥን በአማርኛ ቋንቋ  ስርጭት ጀምረዋል። ችግሩ የሚያወሩትን አማርኛ ለመረዳት ወይ አስተርጓሚ አሊያም ደግሞ ቋንቋ የሚተረጉም ጆሮ ላይ የሚሰካው ትራንስሌተር መግዛት ሊኖርባችሁ ነው። “መቶ” ለማለት “ሞቶ” ይላሉ ። እናንተ በሰበር ዜና “ማን ነው የሞተው? ” ብላችሁ ስትጠብቁ ለካ እነሱ ቁጥር እየጠቀሱ ነው። ግንቦትን “ጉንቨት ” ይሉታል። ብልሽትሽት ያለ ነገር።
2~ህውሃት እንደ ኮሶ የሚመር ሽንፈቷን ግጥም አድርግባ ሰርግባ የፌደራል ዋና ከተማውን ትታ መቀሌ ከገባች ከርማለች ። አንዳንዶቹ ” ቴክኒካል ሪትሪት” አድርጋ እንደገና በድል ለመመለስ ነው ቢሉም እኔ ደሞ ህውሃትን እንደ ድሮው የበላይ ከምትሆን የፓርላማው ተጠሪን አስመላሽ ወልደስላሴን አይን ማብራት ይቀላል እላለሁኝ።
3~ የኢትዮ ሱማሌ ህዝብ ወደ 7 ሚሊዮን ይጠጋል ። የ ሄ ህዝብ ያለው የፓርላማ ወንበር ግን 21 ነው። የትግራይ ህዝብ 5 ሚሊዮን ነው ያለው የፓርላማ ወንበር ግን ካልተሳሳትኩኝ 38 ነው ። በኢህአድግ ምክር ቤትና በስራ አስፈፃሚ ያለው ውክልና ትላልቅ ህዝብ ካላቸው ኦሮሞ ፣አማራና ደቡብ ጋር እኩል ስለሆነ ይሄ በአስቸኳይ መታረም አለበት ።
ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ ይሄን የህገመንግስትና የህግ ጥሰት በአስቸኳይ ማስተካከል ይገባቸዋል።
4~ መለስ ዜናዊ ከመሞቱ በፊት ይመስለኛል የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዜና አንባቢ አንድ የህክምና ዶክተር ( የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት)  ይመስለኛል አቅርቦ ማብራሪያ ከመጠየቁ በፊት ” እስኪ ስምዎን ለህዝቡ ያስተዋውቁልን?  ” ብሎ ይጠይቃቸዋል።
ሃኪሙም ” ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ።” በማለት ሙሉ ስሙን ይናገራል።
ጋዜጠኛው አውቶማቲካሊ ድውክ ብሎ ቁጭ አለ። ሱፍ የለበሰ ድርጭት አከለ ። ከዛ በኋላ እንባ እንባ እያለው ድምፁ እየተንቀጠቀጠ ጥያቄውን ጨረሰ ።
ዛሬ ዶክተር ብርሃኑ ነጋ  ” አሸባሪ ! ” ወንበዴ ! ” እየተባለ በተሰደበበት ፓርላማ “አንቱ ” እየተባለ  ሲሞካሽ ዋለ ። ጊዜ ሲቀያየር እንደዚሁ ነው። ለነገሩ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጎሬላ ውጊያ ፋሽኑ አልፎበታል ወደ አገር ቤት ግቡ ከማለቱ ከወር በፊት እኔ ራሴ ግንቦት 7ቶችን በተመሳሳይ ቋንቋ ” ፋሽኑ አልፎበታል ግቡ ” ብዬ ነበር። ከጠቅላዩ ጋር በዚህ ጉዳይ በቃላት አገላለፅ መመሳሰላችን ገርሞኛል። 🙂
አሁን ፖለቲካው የኢትዮጵያ ህዝብ በሚፈልገው መልኩ  እየተቀየረ ነው ።ገና ግን ብዙ ይቀራል ።ያገኘነውንም ድል ከቀልባሾች መጠበቅ ይገባል ።
ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይንም እንደ ጥሩ ችግኝ ልንከባከበው ይገባል የሚል የግሌ እምነት አለኝ ።
በመጨረሻ ለቅዳሜው መሬት አንቀጥቅጥ የድጋፍ ሰልፍ  መዘጋጄታችንን እንዳይረሳ እላለሁኝ።
Filed in: Amharic