>
5:13 pm - Monday April 19, 0619

በፈርኦን ቤት ላደገው የዘመናችን ሙሴ ቴዲ አፍሮ ሊያቀነቅንለት ነው!!! (ቬሮኒካ መላኩ)

በፈርኦን ቤት ላደገው የዘመናችን ሙሴ ቴዲ አፍሮ ሊያቀነቅንለት ነው!!!

ቬሮኒካ መላኩ
ታዋቂው ኢትዮጵያዊው ከያኒ ቴዎድሮስ ካሳሁን ለጠቅላይ ሚ/ር አቢይ አህመድ እንዳዜመለትና በቅርብ ቀንም ዘፈኑ እንደሚወጣ ሰምቻለሁኝ። ቴዎድሮስ ካሳሁን የኢትዮጵያ ፍቅር እስከ አጥንቱ ድረስ ዘልቆ የሚሰማው አርቲስት ነው። ቴዎድሮስ ለኢትዮጵያ ውለታ ለዋሉ መሪዎችን በችሎታው ለማወደስ ንፉግ አይደለም። ከሌላው  አርቲስት ለየት የሚያደርገውም ይሄው ነው።
ቴዲ አፍሮ  ለእምዬ ምኒልክ ” ጥቁር ሰው ” በማለት አስደምሞናል ። ለአፄ ሀይለስላሴ ” የአፍሪካ አባት ” በማለት አስደንቆናል ። ለአፄ ቴዎድሮስ ” ጎንደር ” በሚል ዜማው መላ ሰውነታችንን እንድነዝረን አድርጎናል።
ቴዲ እንደ ሌሎች አርቲስቶች መሪ በተቀየረ ቁጥር ጃኬቱን እየቀየረ የሚያወድስ ተራ አርቲስት አይደለም።  ቴዲ አፍሮ በጣም ብቻውን ተራራ ነው።
ባለፉት  20  አመታት ቴዲ አፍሮ ” ፍቅር ያሸንፋል ” የሚለውን እንደ ተራራ የገዘፈ ሀይለ ቃል ብቻውን ተሸክሞት ኖሯል ። ስለ ይቅርታ ሰብኳል።  ” ፍቅር ያሸንፋል ” የሚለው  ሀይለ ቃል ቴዲ  ፓተንት ባይወስድበትም በስፋት ለኢትዮጵያውያን ሲያሰርፅ ኖሯል ። ቴዲ አፍሮ ብቻውን ተሸክሞት የኖረውን ” ፍቅር ያሸንፋል” የሚለውን ቃል  ፖለቲከኛውና የወቅቱ የአገሪቱ ጠቅላይ ሚ/ር አቢይ አህመድ ተቀብሎ ለኢትዮጵያውያን እየሰበከ ነው።  የቴዲና የአቢይ አህመድ መናበብ የሚገርም ነው ። ቴዲ በዘፈኑ የነገረንን ዶ/ር አቢይ አህመድ በንግግሩ ያስተላልፋል።ቴዲ አፍሮ ለአቢይ አህመድ ዘፈን ማውጣቱ ተገቢና ወቅታዊም ስለሆነ ሊመሰገን ይገባዋል።
Filed in: Amharic